Get Mystery Box with random crypto!

DW Amharic

Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic D
Logo of telegram channel dw_amharic — DW Amharic
Channel address: @dw_amharic
Categories: News
Language: English
Subscribers: 42.34K
Description from channel

ይህ የዶይቼ ቬለ ይፋዊ የቴሌግራም ገፅ ነው። ትኩስ ዜና፣ በአበይት ፖለቲካዊ፣ ኤኮኖሚያዊ፤ ማኅበራዊ እና ባሕላዊ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩር ትንታኔ ያቀርባል።

Ratings & Reviews

4.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

0

1 stars

0


The latest Messages 6

2023-06-10 16:57:56 Live stream finished (8 seconds)
13:57
Open / Comment
2023-06-10 16:57:48 Live stream started
13:57
Open / Comment
2023-06-09 20:15:55 https://p.dw.com/p/4SOJ7?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
4.6K viewsDW Amharic Team, 17:15
Open / Comment
2023-06-09 20:13:29 https://p.dw.com/p/4SOQX?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
4.4K viewsDW Amharic Team, 17:13
Open / Comment
2023-06-09 20:12:20 https://p.dw.com/p/4SOTD?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
3.4K viewsDW Amharic Team, 17:12
Open / Comment
2023-06-09 20:11:18 https://p.dw.com/p/4SOdc?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
3.3K viewsDW Amharic Team, 17:11
Open / Comment
2023-06-09 20:09:13 *የሱዳንን ጦርነት በመሸሽ በመተማ ዮሐንስ በኩል ብቻ ወደ ኢትዮጵያ የገቡ ከ42 ሺህ በላይ የ70 ሀገራት ዜጎች ወደ የአካባቢያቸው መሸኘታቸውን በአማራ ክልል የምዕራብ ጎንደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽ/ቤት አስታወቀ ። የጽ/ቤቱ ኃላፊ አቶ አበባው በዛብህ ከሱዳን ጦርነቱን ሸሽተው ኢትዮጵያ ለገቡ ሰዎች ስለሚደረገው ድጋፍ ቀጣዩን ለዶይቼ ቬሌ ተናግረዋል ።
«የአደጋ ሥጋት ኮሚሽን ኢትዮጵያውያንን በሙሉ ወደሚፈልጉበት ቦታ ያለክፍያ በነፃ ያጓጉዛል ። ቁጥራቸውን በተመለከተ ወደ ሰባት ሺህ ሊጠጋ ከዚያም በላይ ሊሆን ይችላል ስደተኛ መጠለያ ቦታ ሦስት ቦታዎች ላይ ለይተን አስረክበናል እንደመንግሥት ። አንደኛው መተማ ዮሐንስ ስድስት ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሰፊው ተሠርቶ እዚያ መጠለያ ነው ያሉት ። ሁለተኛው መጠለያ ሠፈር ኩመር ይባላል ። ወደ 56 ሔክታር የሚሆን ቦታ ነው፤ ከድንበር 70 ኪሎ ሜትር አካባቢ ርቀት ላይ ይገኛል ። ሦስተኛው አውላላ የሚባል ቦታ ነው ።»
አሁንም በየቀኑ ከሱዳን በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ እንደሆነም ኃላፊው ተናግረዋል ሲል የባህር ዳር ወኪላችን ዓለምነው መኮንን ዘግቧል ። መሄጃ ለሌላቸው ስደተኞች አስፈላጊው የምግብና ሌሎች ድጋፎች በኢትዮጵያ መንግስትና በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እገዛም እየተደረገ እንደሆነ ኃላፊው ገልጠዋል ። ሱዳን ውስጥ ሚያዝያ 2015 ዓ ም በጀነራል አብድልፈታህ አል ቡረሀን በሚመራው የሱዳን ጦር ሠራዊት እና ጀኔራል መሀመድ ሐምዳ ዳጋሎ ስር በሚገኘው የፈጥኖ ደራሽ ጦር መካከል ሚያዝያ 7 ቀ፣ 2015 ዓ.ም በተጀመረው ጦርነት ቢያንስ 883 ሰላማዊ ሰዎች ተገድለዋል ። 3,800 የሚሆኑት ደግሞ የአካል ጉዳት እንደደደረሰባቸው ተዘግቧል ።

*የሱዳን ተፋላሚዎች ለ24 ሰአታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ዛሬ ማድረጋቸው ተገለጠ ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ ከቅዳሜ ንጋት ይጀምራል ተብሏል ። ተፋላሚዎቹ ለአንድ ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ስለማድረጋቸው በተወካዮቻቸው በኩል በጋራ በሰጡት መግለጫ መጠቀሱን የሳዑዲ ዓረቢያ የውጭ ጉዳይ ሚንሥትር ዐሳውቋል ። «የሱዳን ጦር ሠራዊት እና የፈጥኖ ደራሽ ኃይል (RSF) ከሰኔ 2 ቀን፤ ንጋቱ 12 ሰአት የሚጀምር ለ24 ሰአታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማምተዋል» በሚልም የጋራ መግለጫው ይነበባል ። በዋናነት በዩናይትድ ስቴትስ እና ሳዑዲ ዓረቢያ አሸማጋይነት ሱዳን ውስጥ ከዚህ ቀደም የተደረጉ በርካታ የተኩስ አቁም ስምምነቶች በተደጋጋሚ መክሸፋቸው የሚታወስ ነው ።

*ለሁለተኛ የፕሬዚደንትነት ሥልጣን የሚወዳደሩት የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ሰባት ክሶች እንደቀረበባቸው ተገለጸ ። ክሱ ከምሥጢራዊ የመንግስት ሠነዶች አያያዝ ጋር የተገናኘ ነው ተብሏል ። ዶናልድ ትራምፕ ግን ክሱን አጣጥለዋል ። «ሙሰኛው የባይደን አስተዳደር ክስ እንደቀረበብኝ ለጠበቃዬ ነግሯል ። ያው የተለመደ በሬ ወለደ ነው» ሲሉም ትሩዝ ሶሺያል በተባለው የማኅበራዊ የመገናኛ አውታራቸው ጽፈዋል ። ጠበቃቸው ጂም ትረስቲ ደምበኛቸው ላይ ሰባት ክሶች መቅረባቸውን ለሲኤንኤን የቴሌቪዥን ጣቢያ መናገራቸውን የፈረንሣይ የዜና አገልግሎት (AFP) ዘግቧል ። ስለ ክሱ ጉዳይ ግን ዜናው በወጣበት ወቅት የሀገሪቱ የፍትሕ መሥሪያ ቤት ያለው ነገር የለም ሲል አክሏል ። ዶናልድ ትራምፕ ከ77ኛ ልደታቸው አንድ ቀደም ብሎ ማክሰኞ ሚያሚ ውስጥ ወደሚገኝ ፍርድ ቤት እንዲቀርቡ ጥሪ እንደደረሳቸውም ተናግረዋል ። የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ከተከሰሱባቸው ሰባት ጉዳዮች፦ መንግሥትን ስለመሰለል የሚያወሳውን ሕግ በመጣስ ሆን ብለው ሠነዶች እንዲያዙ አድርገዋል፤ የተሳሳቱ መግለጫዎችን ሰጥተዋል የሚሉት ይገኙበታል ተብሏል ።

የዓለም ዜናውን ሙሉ ዘገባ በድምፅ እዚህ https://p.dw.com/p/4SP25?maca=amh-RED-Telegram-dwcom ማድመጥ ይቻላል ። አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot ማድመጥ ይቻላል።
3.0K viewsDW Amharic Team, 17:09
Open / Comment
2023-06-09 20:09:13 የዐርብ፤ ሰኔ 2 ቀን፣ 2015 ዓ.ም የዓለም ዜና
አርዕስተ ዜና

*ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ 61 የፖለቲካ ፓርቲዎች በአባልነት ያሰባሰበው «የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት» መንግሥት ሀገርን ከከፋ ቀውስ እና ብጥብጥ እንዲታደግ ጠየቀ ።

*ለሁለተኛ የፕሬዚደንትነት ሥልጣን የሚወዳደሩት የቀድሞው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በልደታቸው ዋዜማ ፍርድ ቤት ሊቀርቡ ነው። ማክሰኞ ሚያሚ በሚገኝ ፍርድ ቤት ሰባት ክሶች ይጠብቋቸዋል።

*የሱዳን ተፋላሚዎች ለ24 ሰአታት የሚቆይ የተኩስ አቁም ስምምነት ዛሬ ማድረጋቸው ተገለጠ ። የተኩስ አቁም ስምምነቱ ከቅዳሜ ንጋት ይጀምራል ተብሏል ።

ዜናው በዝርዝር

*የኢትዮጵያ ገዢ ፓርቲ ብልጽግናን ጨምሮ 61 የፖለቲካ ፓርቲዎችን በአባልነት ያሰባሰበው «የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት» ዛሬ አዲስ አበባ ኢሊሌ ሆቴል ውስጥ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፦ መንግሥት ሀገርን ከከፋ ቀውስ እና ብጥብጥ እንዲታደግ ጠየቀ ። የጋራ ምክር ቤቱ በከፍተኛ ደረጃ እየተሸረሸረ ነው ያለውን የፖለቲካ ምህዳር እንዲያሰፋ እና የዜጎችን ሕይወት እና መብት እንዲጠብቅም አሳስቧል ። ግጭት እና የፖለቲካ አለመረጋጋቶች ዜጎችን ለሞት፣ ለአካል መጉደል፣ መፈናቀል እና የሥነ ልቦና ስብራት እየዳረጉ ነው ያለው የፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ በትግራይ ክልል አንፃራዊ ለውጥ መታየቱን ጠቅሷል ። በኦሮሚያ፣ በአማራ እና በጋምቤላ ክልሎች ያለው የሰላም ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ በመሆኑ የፀጥታ እና የደህንነት ተቋማት ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ገለልተኝነት ሕግና ሥርዓትን እንዲያስከብሩ ጠይቋል። ተጨማሪ ዘገባ በዜና መጽሄታችን ይኖረናል ።

*በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ጉጂ ዞን በሕዝብ ማጓጓዣ አገልግሎት ሰጪ ተሽከርካሪ ላይ በተፈጸመ ጥቃት የሁለት ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ አራት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው ተገለጠ ። በጉጂ ዞን ቡሌ ሆራ አቅራቢያ «በዳ መጋጤ» በተባለ ስፍራ በሕዝብ ተሽከርካሪው ላይ የተኩስ እሩምታ የተከፈተው ማክሰኞ (ግንቦት 29 ቀን 2015 ዓ.ም እኩለ ቀን 7፡00 ገደማ) ነው ተብሏል ። ከአደጋው የተረፉ የዐይን እማኞች እና የመንግስት ባለስልጣናት ጥቃቱን ያደረሰው መንግሥት «ሸኔ» በሚል በሽብርተኝነት የፈረጀው እና ራሱን «የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት» ሲል የሚጠራው ሸማቂ ቡድን ነው ብለዋል ። በታጣቂ ቡድኑ በኩል ግን ስለዚህ ጥቃት የተሰጠ ማረጋገጫም ሆነ ማስተባበያ አልተሰማም ። ለደህንነታቸው ሲባል ስማቸው እንዳይጠቀስ የጠየቁ አንድ የዐይን እማኝ ይህን ብለዋል ። «አደጋው የገጠመን በባቱ ከተማ የእንስሳት ልማት ፖኬጅ ስልጠና ለአራት ቀናት ያህል ወስደን ወደ ቤታችን እተመለስን በነበርንበት ነው ፡፡ እየተጓዝን የነበረው በሕዝብ ትራንስፖርት ነበር ፡፡ ድንገት ነው የታጠቁ አካላት ተኩስ ከፍተውብን ስንጓዝበት የነበረውም መኪና ከመንገድ ወጥቶ ጫካ ውስጥ የገባው፡፡ በተከፈተው የተኩስ እሩምታ ሁለት ሰዎች ወዲያው ሲሞቱ አራት ሰዎች ላይ ደግሞ የመቁሰል አደጋ ደርሷል ፡፡ ድንገት የተኩስ እሩምታ ሲከፈትብን ብቻ ነው ያየነው ።»
የምዕራብ ጉጂ ዞን ፀጥታ አስተዳደር ኃላፊ አቶ ገዳ ጎዳና በበኩላቸው ይህ ጥቃት ከመፈጸሙ ከደቂቃዎች አስቀድሞ በመንግስት ጦር እና «ኦነግ ሸኔ» ባሏቸው ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥ እንደነበር ገልጠዋል ።
«ያው ጠላት ሸማቂ እንደመሆኑ አድፍጦ አደጋ የማድረስ ስልት ነው የሚጠቀመው ። ከ300-400 ሜትር ርቀት ውስጥ የመንግስት ታጣቂዎች በቅርቡ ነበሩ ። አደጋው በተፈጠረበ ት በዚህ የበዳ መጋጤ ደን ውስጥ ታጣቂዎች እና የመንግስት ሰራዊት መካከል ተኩስ ነበር ። በዚህ ደን ውስጥ የመንግስት ጦርም ሆነ የሸማቂ ቡድኑ ጦር አለ ። አሁን ችግሩ አልፎ አልፎ የሚያጋጥመን ነው እንጂ መንግስት መንገዱን ተቆጣጥሮ ጥበቃ እያደረገ ነው ።»
በቅርቡ በመንግስት እና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት መካከል በታንዛንያ የተጀመረው የሰላም ድርድር ያለ ተጨባጭ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎ በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ አከባቢዎች በመንግስት እና ሸማቂ ቡድኑ መካከል ግጭት ተባብሷል መባሉን የአዲስ አበባ ዘጋቢችን ሥዩም ጌቱ የላከልን ዜና ይጠቁማል።

*ባለፈው ዓመት ጥቅምት 18 ቀን፣ 2014 ዓ.ም ከምስራቅ ወለጋ ነቀምቴ ከተማ ወደ ሳሲጋ ወረዳ ሲጓዙ በታጣቂዎች የታገቱ 28 የመንግስት ሠራተኞች ከዓመት ከመንፈቅ በኋላም ደብዛቸው ጠፍቶ መቅረቱን የታጋቾቹ ቤተሰቦች ለዶቼቬለ ተናገሩ ። የአራት ልጆት እናት መሆናቸውን እና ባለፈው ዓመት ባለቤታቸው እንደታገቱባቸው የተናገሩ አንዲት የነቀምቴ ከተማ ነዋሪ ከወረዳ እስከ ዞን አስተዳደር አቤት ቢሉም እስካሁን ምንም መፍትሄ አለማግኘታቸውን ገልጠዋል ። ስለ እገታውም ቀጣዩን ብለዋል።
«ጥቅምት 18 ቀን፣ 2014 ዓ.ም ለሥራ በጠዋት እየሄዱ ነበር ። ከባለቤተ ጋር የሄዱ ሌሎች ሰዎች 3 ሰዓት አካባቢ ተመለሱ ። በመንገድ ላይ የታጠቁ ሰዎች የመንገሥት ሠራተኞችን ለይተው ለይተው ማስቀረታቸውን ሌሎችን ደግሞ ወደቤታቹ ሂዱ ብለው እንደመለሷቸው ነገሩን ። በዕለቱ ነው እንግዲህ ታግተው የተወሰዱ ስልክም አልደወሉም በዛው ነው የቀሩት ። ምንም የፖለቲካ ተሳትፎ ያልነበረው የግብርና ባለሞያ ነበር ። አራት ልጆች አሉን አሁን ለፍተኛ ችግር ተጋልጠናል ።»
አንድ የሐይማኖት አባትም ባለቤታቸው ከነቀምቴ ተነስተው ወደ ሳሲጋ ወረዳ እየሄዱ ባሉበት ሰዓት አዳሚ በምትባል ስፍራ መታፈናቸውን በወቅቱ ከእገታ ከተረፉ ሰዎች መስማታቸውን ተናግረዋል ። ሆኖም እስከ ዛሬ ድረስ የት እዳሉ ዐለመታወቁን መረጃውም ከመገናኛ ብዙኃን ዘንድ ሳይደርስ መቆየቱን አክለዋል ። በምስራቅ ወለጋ ዞን የሳሲጋ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዓለማየሁ ኤጄታ 28ቱ የመንግሥት ሠራተኞች መንግስት «ሸኔ» በሚላቸውና ራሳቸውን «የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊ»ት ብለው በሚጠሩ ታጣቂዎች መታገታቸውን ተናግረዋል ። ስለ እገታው ከታጣቂ ቡድኑ በኩል የተሰጠ ማብራሪያ አለመኖሩን የአሶሳ ወኪላችን ነጋሣ ደሳለኝ ዘግቧል ።
2.7K viewsDW Amharic Team, 17:09
Open / Comment
2023-06-09 20:04:01 https://p.dw.com/p/4SMZd?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
2.8K viewsDW Amharic Team, 17:04
Open / Comment
2023-06-09 20:01:56 https://p.dw.com/p/4SOgp?maca=amh-RED-Telegram-dwcom
አስተያየት ለመስጠት፣ ጥቆማ ለማድረስ ይኽን ቦት ይጠቀሙ @dwamharicbot
3.0K viewsDW Amharic Team, 17:01
Open / Comment