🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት) S
Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Channel address: @nationalexamsresult
Categories: Education
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 41.40K
Description from channel

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 296

2021-03-22 18:49:20 “የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ድርሻ እና አስተዋፅኦ ለሀገራዊ ብልጽግና” በሚል መሪ ቃል ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አመራሮች በዘርፉ ፖሊሲ እና ስትራቴጂ ላይ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

==================================================

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ባዘጋጀው የልማት ፖሊሲ፤ የፖሊሲው ማስተግበሪያ ፕሮግራሞች እና የቀጣይ 10 ዓመታት የልማት መሪ እቅድ እና ቁልፍ የውጤት አመልካች / KPI / ዙሪያ ሥልጠና እየተሰጠ ይገኛል፡፡

የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ክቡር ፕሮፌሰር አፈወርቅ ካሱ ፖሊሲና ስትራቴጂው ለሀገሪቱ የብልጽግና ጉዞ ሚናው የላቀ መሆኑን የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እንዲገነዘቡና የየራሳቸውን ድርሻ እንድወጡ ታሳቢ መደረጉን ተናግረዋል፡፡

ፖሊሲው ከሀገራዊ የአስር አመቱ እቅድ መነሻ ያደረገ በመሆኑ የጋራ በማድረግ በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መተግበር አስፋላጊ በመሆኑ ከአመራሮች ጋር ውይይት ማድረግ እንዳስፈለገ ፕሮፌሰር ሚኒስቴር ዴኤታዉ አክለዋል፡፡

የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተሳታፊ አመራሮች በበኩላቸው በፖሊሲ፣ ስትራቴጂ እና መሪ እቅዱ ዙሪያ ሥልጠና ተዘጋጅቶ እንዲወያዩበት መደረጉ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚረዳቸው ተናግረዋል፡፡

በሥልጠና ፕሮግራሙ የሁሉም የግል ከፍተኛ ተቋማት፣ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበር፣ የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ኤጀንሲ ፣ የተጠሪ ተቋማት እና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል፡፡

በሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀዉ ሥልጠና በአዋጅ 1097/2011 እና አዋጅ 1152/2011 የተቀመጡ ቁልፍ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ተልዕኮዎች ላይ ያተኮረ ሲሆን ከመጋቢት 13-14/7/2013ዓ.ም ለሁለት ቀናት ይሰጣል

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
3.4K viewsedited  15:49
Open / Comment
2021-03-22 13:11:54
"...እሳቱ በሰው ኃይል ይጠፋል ብሎ ማሰብ የማይቻልበት ደረጃ ደርሷል" -ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ደረጄ ብርሃኑ

ከትላንት ጀምሮ በደብረ ወገግ አሰቦት ገዳም የሰደድ እሳት ቃጠሎ ተነስቷል።

በደብረ ወገግ አሰቦት ገዳም የተነሳው ሰደድ እሳት ለማጥፋት ከጭሮ /አሰበተፈሪ/፣ አሰቦት መኢሶ እና ከአካባቢው ወረዳዎች ወደ ሥፍራው የተጓዙ ምእመናን ከፍተኛ ጥረት ቢያደርጉም እሳቱ ሌሊቱን በነፋስ ታግዞ ወደ ገዳሙ ክልል እየሰፋ መምጣቱን የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ደረጄ ብርሃኑ ለኢኦተቤ ቴሌቪዥን ገልጸዋል፡፡

በየዓመቱ ከየካቲት ወር ጀምሮ በሚኖርው ሞቃታማ እና ደረቃማ የአየር ሁኔታና ክሰል ማክሰልን በመሰሉ የተለያዩ የሰው ሰራሽ ምክንያቶች የሰደድ እሳት የገዳሙን ክልል እንደሚያጠቃ የተናገሩት የምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ሊቀ ኅሩያን ቀሲስ ደረጀ ትላንት ምክንያቱ በውል ባልታወቀ ሁኔታ የሰደድ እሳቱ እንደተነሳ እና ገላግሌ ከሚባለው ስፍራ በመነሳት መስፋፋቱ ሪፖርት አንደቀረበላቸው ተናግረዋል፡፡

ሀገረ ስብከቱ ምእመናንን በማስተባበር ሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር እየሞከረ እንደሆነ ያስታወቁት ሊቀ ኅሩያን ደረጄ የመንግሥት የጸጥታ መዋቅር ወደ ሥፍራው ደርሶ ተገቢውን እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡

እሳቱ በሰው ኃይል ይጠፋል ብሎ ማሰብ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን ያስታወቁት ሊቀ ኅሩያን ደረጀ መንግሥት ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ሌሎች አማራጮችን መጠቀም ይገባዋል ብለዋል፡፡

የደብረ ወገግ አሰቦት ገዳም ጥንታዊ ቅርሶችና እድሜ ጠገብ እጽዋት እና ሀገር በቀል ዛፎች እንዲሁም ብርቅዬ የዱር እንስሳት ያለበት በብዝኃ ሕይወት የበለጸገ ገዳም ነው፡፡


ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
4.5K viewsedited  10:11
Open / Comment
2021-03-22 12:56:57 #በሳይንስና_ከፍተኛ_ትምህርት_ፖሊሲዎችና_ስትራቴጂዎች_ላይ_በሀዋሳ_ዩኒቨርሲቲ_ውይይት_ተካሄደ
ለሁለት ቀናት በተደረገው የውይይትና የምክክር መድረክ መክፈቻ ላይ ዶ/ር አያኖ በራሶ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት እንደተናገሩት የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር ከተቋቋመ ጀምሮ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴር አዋጅ፣ ደንቦች፣ መመሪያዎችና ፖሊሲዎች ወጥተው ተግባራዊ የሆኑ ሲሆን በዛሬው ዕለትም በቅርቡ ተግባራዊ የሆኑ እና በሚሆኑ የሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲዎች፣ ስትራቴጂዎችና የ10 እና 5 ዓመት ዕቅድ ላይና በዩኒቨርሲቲው የ10 እና 5 ዓመት ዕቅድ ላይ ከከፍተኛ፣ ከመካከለኛና ዝቅተኛ አመራሮች ጋር ለመወያየትና ለመምከር መሆኑን ገልጸው በቀጣይም ከሁሉም መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ጋርም ውይይጥ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ ፕሬዚዳንቱ አክለውም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የምርምር ዩኒቨርሲቲ ተብለው ከተለዩት አንዱ እንደመሆኑ የቀጣይ 10 ዓመት ዕቅድ ስናዘጋጅም ምርምርን መሰረት በማድረግና የልህቀት ማዕከሎች ከማጎልበት አንጻር ሲሆን አመራሮች በስራቸው ያሉትን ስራዎችና ሰራተኞች በአግባቡ ለማስተዳደር በዕለቱ የቀረቡትን የማስፈጸሚያ ስልቶች መረዳትና ማወቅ ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
በዕለቱ የከፍተኛ ትምህርት ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ያቀረቡት ዶ/ር ፍስሃ ጌታቸው እንደተናገሩት ባለፉት 20 ዓመታት ዩኒቨርሲቲዎች እየተስፋፉ የመጡ ቢመጡም የዛኑ ያክልም ከአግባብነት፣ ከተደራሽነት፣ ከአካታችነት፣ ከትምህርት ጥራትና የፖሊሲ አቅጣጫ ከማስቀመጥ አኳያ ችግሮች በመኖራቸው ገበያው የሚፈልገውን እና አካታች የሆነ የሰው ኃይል በበቂ ቁጥርና ጥራት ማፍራት አለመቻሉን ተናግረው ዩኒቨርሲቲው እስካሁን ጥራትና ብቃት ያላቸውን ምሩቃኖች ለማፍራት ብቃት ያላቸውን መምህራንን በመቅጠርና ብቃታቸውን ለማሳደግ እና ገበያው የሚፈልገውን ምሩቃንን ከማፍራት አንጻር እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ዶ/ር ታፈሰ ማቲዎስ የም/ቴ/ሽ/ም/ፕሬዚዳንት የሳይንስ ፖሊሲዎችና ስትራቴጂዎች ከምርምርና ከቴክኖሎጂ አንጻር የተዘጋጀ ሰነድ ባቀረቡ ወቅት የኢትዮጵያ ሳይንስ ፖሊሲ የትኩረት መስኮች የሰው ሃብት ልማት፣ የኢንተርፕራይዝ ልማት፣ ሳይንሳዊ ምርምርና ፈጠራ፣ መሰረተ ልማትና ግብዓት፣ የእውቀት/ሀብት አያያዝ ስርዓት፣ ፋይናንስና ማበረታቻ ስርዓት እና ሃገራዊ፣ አህጉራዊና ዓለምአቀፋዊ አጋርነት መሆናቸውን ገልጸው በየአንዳንዱ ስርም የሚገኙትን የተለያዩ ግቦችና የማስፈጸሚያ ስልቶችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
4.0K viewsedited  09:56
Open / Comment
2021-03-22 12:56:12
ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር በዚህ አመት 200 የአካቶ ትምህርት መስጫ ማዕከላት ተቋቁመዋል።
-----------------
የትምህርት ሚኒስቴር በልዩ ድጋፍ መስጫ ማዕከላት ዙሪያ ለርዕሳነ መምህራንና ተዘዋዋሪ መምህራን ስልጠና ሰጥቷል።

በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘውን የልዩ ፍላጎት ያላቸው ተማሪዎችን ተደራሽነት ለማረጋገጥ የትምህርት ሚኒስቴር በዚህ አመት 200 የአካቶ ትምህርት ድጋፍ መስጫ ማእከላትን አቋቁሟል።

ማዕከላቱ እስከ 35 የልዩ ፍላጎት ተማሪዎችን ማስተናገድ የሚችሉ ናቸው።

ስልጠናው የተሰጠው ርዕሳነ መምህራንና ተዘዋዋሪ መምህራንን ማዕከላቱን በአግባቡ በማደራጀት በተገቢው መንገድ መጠቀም እንዲችሉ ለማድረግ ነው።

የልዩ ድጋፍና አካቶ ትምህርት ዳይሬክተር አቶ ተኽላይ ገ/ ሚካኤል በአገሪቱ አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ እድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ሁሉም ህጻናት የመማር መብታችው እንዲረጋገጥ በትኩረት እየተሰራ ቢሆንም አሁንም የአካል ጉዳተኛ ህጻናት የትምህርት ተሳትፎ በዝቀተኛ ደረጃ ላይ ይገኛል ብለዋል።

ፍትሀዊ የትምህርት ተደራሽነት ማረጋገጥ የሁሉም የትምህርት ስራ ባለድርሻዎች መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በተለይም ወላጆች ልጆቻቸውን ወደ ትምህርት ቤት በመላክ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል

የትምህርት ፍትሀዊነትን በማረጋገጥ የአካል ጉዳተኞችን የትምህርት ተሳትፎ ለማጎልበት ትምህርት ሚኒስቴር የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል።

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
4.1K viewsedited  09:56
Open / Comment
2021-03-22 06:13:00
እንኳን ደስ ያለን
የኢትዮጵያ ተወካይ የነበረው Andalus team ከ አዳማ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ወደ አለም ሻምፒዮና አልፏል

Congratulations
Andalus team from Adama Science and
Technology University (ASTU) has passed to the 2021 World Final contest.

#luxoregypt
#Andalus
#ACPC_2020
#EthCPC

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
2.8K views03:13
Open / Comment
2021-03-21 21:55:12
ኢትዮጵያን ወክለው ግብፅ ላይ የሚካሄደውን Africa and Arab Colligative programming contest (ACPC) እየተወዳደሩ ያሉ የ ሀገራችን ቡድኖች

Ethiopian Competitive Programming teams
Andalus (ASTU)
KelemMeda (Wollo University )
code linguist(Debre berhan university)
are now in Luxor, Egypt support them on
https://m.facebook.com/EthiopiaCPC

ቡድኖቻችን ጥሩ ውጤት የሚያመጡ ከሆነ ፈረንሳይ ላይ ለሚዘጋጀው አለም አቀፍ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የፕሮግራሚንግ ውድድር የሚያልፉ ይሆናል።

መልካም እድል

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
3.9K viewsedited  18:55
Open / Comment
2021-03-21 21:54:48
አዲስ ዋጋዉ ተመጣጣኝ ከዚህ በፊት ያልተለመደ
ለቤተሰብ ለጓደኛ ለፋቅረኛ የሚወዱትን ዘፍኝ ፎቶ... የተለያዩ ነገሮችን በመስታወት ላይ በማሰራት ጥሩ ማስታወሻ ስጦታ በመስጠት የሚወዱትን ሰዉ ያስደስቱ።

#Price 650
Contact on Telegram @Henak_21
0924848164
3.5K views18:54
Open / Comment
2021-03-21 21:52:21
ጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ለምትወስዱ ፦

የብቃት ምዘና ፈተናው ከመጋቢት 20-24/2013 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን የፈተና ፕሮግራሙ ፦

• ነርሲንግ - 20/07/2013 ዓ.ም

• ጤና መኮንን - 21/07/2013 ዓ.ም

• ህክምና እና ሜዲካል ላብራቶሪ ሳይንስ - 22/07/2013 ዓ.ም

• ፋርማሲ እና አንስቴዥያ - 23/07/2013 ዓ.ም

• ሚድዋይፈሪ - 24/07/2013 ዓ.ም

* የብቃት ምዘና ፈተናውን ለመጀመሪያ ጊዜ የሚወስዱ ተመዛኞች በቀጥታ በተማሩበት ተቋም ወይም የተማሩበት ተቋም በሚገኝበት ከተማ በሚገኝ የመፈተኛ ጣቢያ የሚመደቡ ይሆናል፡፡

* ለዳግም ምዘና /Re-Exam/ በOnline Registration የተመዘገቡ እና ከአዲስ አበባ ውጪ ያሉ የመፈተኛ ከተሞችን የመረጡ ተመዛኞች በቀጥታ በመረጡት ከተማ በሚገኝ የምዘና ጣቢያ የሚመደቡ ይሆናል (የመፈተኛ ከተሞችንና ጣቢያዎችን ይህን ተጭነው ይመልከቱ telegra.ph/MoHEthiopia-03-21)

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
3.7K viewsedited  18:52
Open / Comment
2021-03-21 17:42:46
ዜና እረፍት

የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ መምህር የነበሩት አቶ ተገኘወርቅ ገ/መድህን ወልዴ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ።

መምህር ተገኘወርቅ ከ2006ዓ/ም ጀምሮ በግብር ኮሌጅ በመምህርነት ተቀጥረው ሲያገለግሉ የቆዩ ሲሆን ለዶክትሬት ዲግሬ ትምህርታቸውን በሀራማያ ዩኒቨርሲቲ እየተከታተሉ ባበት ወቅት በገጠማቸው ህመም ምክንያት በሃራማያ ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው ሊሻላቸው ባለመቻሉ መጋቢት 11/2013ዓ/ም ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል።

የቀብር ስነ-ስርዓታቸውም ባልደረቦቻቸውና ወዳጅ ዘመዶቻቸው በተገኙበት ከደብረብርሃን ከተማ በ17ኪሎሜትር ርቀት በትውልድ ስፍራቸው መጋቢት 13/2013ዓ/ም ይፈጸማል።

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በውድ መምህሩ ተገኘወርቅ ገ/መድህን ህልፈተ ህይወት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለቤተሰቦቹ መጽናናትን ይመኛል።

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
5.5K viewsedited  14:42
Open / Comment
2021-03-20 21:05:42
መቅደላ አምባ ዩኒቨርሲቲ ስለEconomics ዲፓርትመንት ይሄን ለተማሪዎቹ አጋርቷል

#SHARE
መረጃው ለሌሎችም እንዲደርስ ያጋሩ

ለተጨማሪ መረጃ ቻናላችንን ተቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
2.6K viewsedited  18:05
Open / Comment