Get Mystery Box with random crypto!

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Channel address: @nationalexamsresult
Categories: Education
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 41.92K
Description from channel

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 2

2024-02-08 19:57:28 የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡

(ቀን ጥር 30/2016 ዓ.ም)

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.2K views16:57
Open / Comment
2024-02-08 08:45:53
#ማስታወቂያ

ለድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ

የካቲት 6/2016 ዓ.ም ጀምሮ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና  ለመፈተን በመጠባበቅ ላይ ለምትገኙ የ ድጋሚ (Re-exam) ተፈታኞች በሙሉ የመፈታኛ የይለፍቃል (Password) ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

1. በምዝገባ ወቅት በሞላችሁት email በኩል

2.  https://exam.ethernet.edu.et  ላይ በመግባት የከፈላችሁበትን Transaction Number በማስገባት እንዲሁም

3. ከተመደባብችሁብት የመፈተኛ ተቋም ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ
• ለመጀመሪያ ጊዜ የመዉጫ ፈተና የምትፈተኑ እጩ ተመራቂዎች የይለፍቃል (Password) የምታገኙት ከምትማሩበት ወይም ከተመደባብችሁበት የመፈተኛ ተቋም ብቻ መሆኑን እናሳውቃለን።

• ሁሉም ተፈታኞች የሞዴል ፈተናን እስከ  የካቲት 5/2016 ዓ.ም መውሰድ ይኖርባቸዋል።

ትምህርት ሚኒስቴር

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
14.2K viewsedited  05:45
Open / Comment
2024-01-31 21:38:02 #Update

የ2016 ዓ.ም አጋማሽ ዓመት የመውጫ ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ተራዝሟል።

የመውጫ ፈተናው ከጥር 27 እስከ የካቲት 01/2016 ዓ.ም ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም።

ትምህርት ሚኒስቴር አዲስ ይፋ ባደረገው መርሐግብር ፈተናው ከየካቲት 06 እስከ 09/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ታውቋል።

ለአዲስ ተፈታኞች ሞዴል ፈተና ከጥር 27 እስከ 30/2016 ዓ.ም እንደሚሰጥ ቲክቫህ ከትምህርት ሚኒስቴር ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የተፈታኞች ዝርዝር ለከፍተኛ ትምህርት ተቋማቱ በቀጣይ ቀናት እንደሚላክም ተገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.0K viewsedited  18:38
Open / Comment
2023-12-19 19:33:28
ለጥናትና ምርምርዎ እገዛ ይፈልጋሉ?
    አዎ ከሆነ መልስዎ!
በመንግስትም ሆነ በግል ዩኒቨርሲቲ/ኮሌጅ በዲፕሎማ፣ዲግሪ እና በማስተርስ ፕሮግራም ለምትማሩ እና ትምህርታችሁን ጨርሳችሁ የምርቃት ጊዜያችሁን በጉጉት ለምትጠብቁ ሁሉ ስለ ጥናትና ምርምር በቂ እዉቀትን በመያዝ የመመረቂያ ፅሁፋችሁን ተመራጭ እና ተወዳጅ አድርጋችሁ በመስራት በጥሩ ዉጤት ትመረቁ  ዘንድ እናግዝዎታለን፡

If you need support related to:    
1 Assignment / አሳይመንት
2 Research / ሪሰርች
3 Proposal / ፕሮፖዛል
4 Term Paper /  ተረም ፔፐር
5 Case study/ ኬዝ ስተዲ
6 Article Review
7  Mini research
8  Business plan
9  Environmental impact assessment [EIA]

Any other Questions
Contact us via
@ResearcherETH
@ResearcherETH
@ResearcherETH
12.6K viewsedited  16:33
Open / Comment
2023-12-12 12:25:48
አዲግራት ዩኒቨርስቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን 832 አዲስ ተማሪዎች መቀበሉን አስታወቀ።

ዩኒቨርስቲው በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን ከ1 ሺሕ 500 በላይ ተማሪዎች ታህሳስ 6 ቀን 2016 ዓ.ም እንደሚያስመረቅም ተመላክቷል።

የዩኒቨርስቲው የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር ዮሐንስ ከበደ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎቹን የተቀበለው የመመገቢያ፣ የመማሪያ፣ የመኝታ እና ሌሎች ለመማር ማስተማር ሥራው አስፈላጊ የሆኑ የዝግጅት ሥራዎችን ካጠናቀቀ በኋላ መሆኑን ተናግረዋል።

ከዚህ በተጨማሪ የዩኒቨርስቲውን ቅጥር ግቢ በማስዋብና በማፅዳት ተማሪዎቹን መቀበሉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።

ዩኒቨርስቲው ትምህርታቸውን በተለያዩ ምክንያቶች አቋርጠው ከነበሩ ከ5 ሺሕ በላይ ተማሪዎች መካከል ዳግም ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 1 ሺሕ 500 ተማሪዎችን የፊታችን ቅዳሜ እንደሚያስመርቅም ዮሐንስ አመልክተዋል።

የመቀሌ እና የአክሱም ዩኒቨርስቲዎች በተያዘው የትምህርት ዘመን የሚያስተምሯቸውን ከ2 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት መቀበላቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
12.7K viewsedited  09:25
Open / Comment
2023-12-09 12:47:13
የኢትዮጵያ አየርመንገድ አቪዬሽን ዩንቨርስቲ ከ600 በላይ በተለያዩ መስኮች ያስለጠናቸውን ተማሪዎችን በማስመረቅ ላይ ይገኛል።

በዛሬው የምርቃት ፕሮግራም በአውሮፕላን አብራሪነት በአውሮፕላን ጥገና እና መስተንግዶ ያሰለጠናቸውን ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

በምርቃት ስነስርዓቱ የኢትዮጵያ አየርመንገድ ዋና ስር አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰውን ጨምሮ የኢትዮጵያ አቪዬሽን ዩንቨርስቲ ፕሬዚዳንት አቶ ካሴ ይማም የተማሪዎች ወላጆች በተገኙበት በኢትዮጵያ አየርመንገድ ውስጥ ፕሮግራሙ እየተካሄደ ይገኛል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
12.6K views09:47
Open / Comment
2023-11-16 20:12:16
በአማራ ክልል በጸጥታ ችግር ምክንያት የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ የዓመቱን የመማር ማስተማር ሒደት ለማሻሻል ጥናት እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ፡፡

በክልሉ ምስራቅ፣ ምዕራብ እና ሰሜን ጎጃም ዞኖች እስካሁን ትምህርት አለመጀመሩን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) ለአሚኮ ተናግረዋል። 

በጸጥታ ሥጋት ምክንያት ከተገለፁት ዞኖች ውጭ በሚገኙ የክልሉ አካባቢዎች 60 በመቶ የአንደኛ ደረጃ እና 55 በመቶ የ2ኛ ደረጃ ተማሪዎች ብቻ በመማር ላይ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

በክልሉ በየጊዜው ሰላም በሚኾንባቸው አካባቢዎች ከጸጥታ መዋቅሩ እና ከማኅበረሰቡ ጋር በመቀናጀት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ እየተሠራ ነው ብለዋል።

የባከነውን የትምህርት ጊዜ ለማካካስ ቢሮው የዓመቱን የትምህርት ሥርዓት እንደገና ለማሻሻል ጥናት እያደረገ  እንደሚገኝም ኃላፊዋ ጠቁመዋል።

በተለይ በዚህ ዓመት የክልል እና ሀገር አቀፍ ፈተና ለሚወስዱ የ6ኛ፣ የ8ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የባከኑ ጊዜያትን በልዩ ሁኔታ ለመሸፈን ከመምህራን እና ርዕሰ መምህራን ጋር ውይይት እየተደረገ መኾኑን ገልጸዋል፡፡

አሚኮ

⊰  ㅤ    ⫹⫺ㅤ     ⎙ㅤ     ⌲ ⊱
࿙ ᴸⁱᵏᵉ    ˢᵘᵖᵖᵒʳᵗ    ˢᵃᵛᵉ     ˢʰᵃʳᵉ ࿚

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
13.2K viewsedited  17:12
Open / Comment
2023-11-09 14:42:19
#JigjigaUniversity

ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ነባር የመጀመሪኛ ዲግሪ አንደኛ ዓመት (Freshman) ወይም በ2015 ዓ.ም መደበኛ የሪሚዲያል ፕሮግራም አዲስ ገቢ ተማሪዎች የምዝገባ ቀን ህዳር 06 እና 07 /2016 ዓ.ም መሆኑን አሳውቋል፡፡

በመሆኑም በተጠቀሱት ቀናት ብቻ በአካል በመቅረብ እንድትመዘገቡ ዩኒቨርሲቲው አሳስቧል፡፡

ወደ ተቋሙ ስትሔዱ የስፖርት ትጥቅ፣ አንሶላ እና ጉርድ ፎቶግራፍ ልትይዙ እንደሚገባ ዩኒቨርሲቲው አስታውሷል፡፡

ለተጨማሪ መረጃ፦ regi@jju.edu.et / info@jju.edu.et
የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
13.0K viewsedited  11:42
Open / Comment
2023-08-29 10:57:47
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሚቀጥለው የትምህርት ዘመን ተማሪዎችን የሚቀበልበት መስፈርት እንደሚከተለው ይሆናል፡-

1. እንደማንኛውም ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ወጪያቸውን በመንግስት የሚሸፈንላቸውን ተማሪዎችን ፈትኖ ይቀበላል፣

2. በአሁኑ ሰዓት በማታው ክፍለ ጊዜ (Extension) በግል እየተማሩ እንደሚገኙ ተማሪዎች በመደበኛው ክፍለ ጊዜም (Regular) ተመሳሳይ ተማሪዎችን ተቀበሎ በመጠነኛ ክፍያ የሚያስተምር ይሆናል፣

3. ዩኒቨርሲቲው በፊት ከነበረው ከትምህርት ሚኒስቴር ከሚላክለት የተማሪዎች ቅበላ ውጭ በልዩነት ፈትኖ ተማሪዎችን ቢቀበልም ከዚህ በፊት በመንግስት ከሚመደብለት የተማሪዎች ቁጥር ያነሰ አይሆንም፤

4. አዋጁ በግልጽ እንዳስቀመጠው ሁሉንም የኢትዮጵያ ተማሪዎችን ታሳቢ ያደረገ የትምህርት ተቋም እንደሆነ ዩኒቨርሲቲው ይገልፃል

ይሁንና በአሁኑ ሰዓት በተለያዩ ድህረ-ገፆች ላይ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሐብታሞች መማሪያ ብቻ ይሆናል ተብሎ የሚናፈሰው ወሬ ሀሰተኛና የህግ አግባብነት የሌለው መሆኑን ዩኒቨርሲቲው ያሳውቃል፡፡

በመሆኑም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሁሉም ኢትዮጵያዊ መዳረሻ ፣ የእውቀት መገብያ መናኸሪያ እንዲሆን እንጂ ራስ ገዝ አስተዳደር ያስፈለገው የገንዘብ አቅም ያላቸው ተማሪዎችን ብቻ ተቀብሎ የሚያስተምር ተቋም እንዳይሆን ታስቦ እንደሆነ ለመግለጽ እንወዳለን፡፡
ይህ ማለት አንድ ተማሪ ወደ ተቋሙ ለመማር አስቦ ሲመጣ እንደማንኛውም ተማሪ ከክፍያው በፊት የተቋሙን የትምህርት መመዘኛ መስፈርቶች (Admission paper) ሲያገኝ ብቻ ይሆናል::

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
16.4K viewsedited  07:57
Open / Comment
2023-08-28 13:26:24
በአማራ ክልል የ2016 ትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከነገ ነሐሴ 23/2015 ዓ.ም ጀምሮ ይካሔዳል፡፡

የተማሪዎች ምዝገባ እስከ ጳጉሜን 03/2015 ዓ.ም ደረስ ይከናወናል፡፡

በክልሉ የሚገኙ ትምህርት ቤቶች መስከረም 02/2016 ዓ.ም ይከፈታሉ የተባለ ሲሆን መስከረም 14/2016 ዓ.ም የመማር ማስተማር ሥራ ይጀምራል ተብሏል፡፡

በአማራ ክልል 6 ነጥብ 3 ሚሊዮን ተማሪዎች ምዝገባ ያደርጋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት
@NATIONALEXAMSRESULT
12.8K viewsedited  10:26
Open / Comment