Get Mystery Box with random crypto!

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Channel address: @nationalexamsresult
Categories: Education
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 41.92K
Description from channel

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 10

2023-05-10 16:46:59
የግል ትምህርት ቤቶች የክፍያ ጭማሪ እያማረራቸው መሆኑን ወላጆች ተናገሩ

ለኢቲቪ አስተያየታቸውን የሰጡት ወላጆች፣ ገቢያችን ሳይጨምር በየዓመቱ የሚደረገው የትምህርት ቤቶቹ ጭማሪ ከአቅም በላይ ሆብናል፤ እዚህ ላይ ቁጥጥር መደረግ አለበት ብለዋል።

የአዲስ አበባ ከተማ የግል ትምርት ቤቶች አሠሪዎች ማኅበር በበኩሉ፣ ትምህርት ቤቶቹ በኮቪድ በደረሰባቸው ከፍተኛ ኪሳራ እና በ2015 ዓ.ም ጭማሪ እንዳያደርጉ መከልከላቸው ገበያው ላይ ለመቆየት የግድ ጭማሪ ለማድረግ እንሚያስገድዳቸው ገልጿል።

ትምህርት ቤቶች ዝግ በሚሆኑበት ሐምሌ እና ነሐሴ ለመምህራን የሚከፈለው ክፍያም ግንዛቤ ውስጥ መግባት አለበት ያለው ማህበሩ ግብአቶችን ለማቅረብ አሁን ያለው የገበያ ዋጋ ትልቅ ተግዳሮት መሆኑንም ገልጿል።

በዚህም የተሻለ የትምህርት አካባቢን ለመፍጠር እና የተሻለ አገልግሎት ለመስጠት እንዲሁም የሚፈልገውን ትርፍ አግኝተው በገበያው ውስጥ ለመቆየት የክፍያ ማስተካከያ ግዴታ ነው ብሏል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
4.1K viewsedited  13:46
Open / Comment
2023-05-10 16:45:32
ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚኒስትሮች ጋር ተወያዩ

ረቡዕ ግንቦት 2 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከአለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ ጎን ለጎን ከተለያዩ አገራት የትምህርት ሚኒስትሮች ጋር የፓናል ውይይት አካሂደዋል።

በውይይታቸውም ኢትዮጵያ በትምህርት ዘርፉ ላይ እያደረገችው ያለውን ለውጥ እና ሥራ ያብራሩ ሲሆን፤ በአጠቃላይ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝም አንስተዋል።

የዘንድሮው አለም አቀፍ የትምህርት ጉባኤ <<አዲስ ጅማሮ፡ የመማር ባህልን ማሳደግ፣ የመቋቋም አቅምን መገንባት፣ ዘላቂነትን ማሳደግ። በንድፍ ሃሳብ የተደገፈ ጠንካራና የተሻለ ትምህርት>> በሚል መሪ ቃል በብሪታኒያ እየተካሄደ ይገኛል።

ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤ በትናንትናው ዕለት ከብሪታኒያ የልማትና የአፍሪካ ጉዳዮች ሚኒስትር ዴኤታ አንድሪው ሚቼል እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ የልጃገረዶች ትምህርት ልዩ መልዕክተኛ ከሆኑት ሄለን ግራንት ጋር በትምህርት ዘርፍ ያለውን ትብብር የበለጠ ማጠናከር በሚቻልበት ሁኔታ ላይ መወያየታቸውም ተገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
3.6K viewsedited  13:45
Open / Comment
2023-05-10 16:45:31 #Update
የቀድሞ የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ጫላ ዋታን (ዶ/ር) ጨምሮ 15 ግለሰቦች ላይ የሙስና ወንጀል ክስ ተመሰረተ

ረቡዕ ግንቦት 2 ቀን 2015 (አዲስ ማለዳ) የቡሌ ሆራ  ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጫላ ዋታን (ዶ/ር) ጨምሮ 15 ተከሳሾች ላይ ከ195 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ የሙስና ወንጀል በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት ክስ ተመስርቷል።

ተከሳሾቹ በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ያለመከሰስ መብታቸው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የተነሳው  በቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት ጫላ ዋታ (ዶ/ር)፣ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት ታምሩ ኦኖሌ፣ የአስተዳደር እና የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ፕሬዚዳንት ሮባ ደንቢ (ዶ/ር)፣ የቢዝነስና ተቋማዊ ልማት ምክትል ፕሬዚዳንት አብርሐም ባያብል (ኢ/ር)፣ የግዢ ዳይሬክተር ሊበይ ገልገሎ፣ የግዢ ዳይሬክተር ቦሩ ህርቦዬ፣ የዩኒቨርሲቲው መምህርና የቢኤች ዩ አማካሪ ለታ ድሪባን ጨምሮ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጮችና የቢዳሩ ኮንስትራክሽን ሥራ አስኪያጆች ይገኙበታል።

በተከሳሾቹ ላይ የፍትሕ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ አራት ተደራራቢ የሙስና ወንጀል ክሶችን መመስረቱ ነው የተገለጸው።

በዚህም ከ1ኛ እስከ 6ኛ ተራ ቁጥር ያሉት ተከሳሾች የዩኒቨርሲቲው አመራርና የማኔጅመንት አባል በመሆን ሲሰሩ የመንግሥት ግዢ አዋጅን በመተላለፍ በ2012 በያዙት ቃለ ጉባኤ መሰረት ሕግን ባልተከተለ መልኩ ያለአግባብ "ቢኤች ዩ" ለተባለ አማካሪ ግዢው በቀጥታ እንዲፈጸም  በማኔጅመንት ውሳኔ ማስተላለፋቸው ተጠቁሟል፡፡

በተጨማሪም ዩኒቨርሲቲው ውል ሲዋዋል ዩኒቨርሲቲውን በመወከል የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት 1ኛ ተከሳሽ ውል ሰጪ ሆነው 7ኛ ተከሳሽ ውሉን በመፈረም በ5ኛ ተከሳሽ ትዕዛዝ መሰረት በአንደኛ ተከሳሽ ሥም ለተመዘገበው አማካሪ ድርጅት ያለአግባብ ክፍያ እንዲፈጸም ማድረጉን ዐቃቤ ህግ በክሱ ጠቅሷል።

በሌላ በኩል  የዩኒቨርሲቲውን የመተዳዳሪያ እና የግዢ አዋጅ በመተላለፍ የ14 ተሽከርካሪዎችና ማሽነሪዎችን  ግዢ በመፈጸምና 116 ሚሊየን 389 ሺሕ 964 ብር ማሽነሪዎችን በስጦታ ያገኙ በማስመሰል ያለአግባብ 12ኛ፣ 13ኛ እና 14ኛ ተከሳሾች በተሽከርካሪ ግዢ ጥቅም ማግኘታቸው ተመላክቷል።

ተከሳሾቹ ሰኔ 10/2012 በቀጥታ ግዢ እንዲፈጸም ውሳኔ በማስተላለፍ ከሌሎች ተከሳሾችና ከሥራ ተቋራጮች ያለአግባብ ካለ ግልፅ ጨረታ ግዢ በመፈጸም በመንግስት ላይ 195 ሚሊየን ብር በላይ ጉዳት አድርሰዋል ሲል ዐቃቤ ሕግ በዋና እና በልዩ ወንጀል ተካፋይ በመሆን ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል ተደራራቢ የሙስና ወንጀል ክስ አቅርቦባቸዋል።

በዚህ መልኩ የተመሰረተባቸው የክስ ዝርዝርም በችሎት ለተከሳሾቹ እንዲደርስ ተደርጓል፡፡

ተከሳሾቹ ከጠበቃቸው ጋር ተማክረው የፊታችን ግንቦት 7/2015 ፍድር ቤት ቀርበው ክሱን በንባብ ለማሰማት ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
3.8K viewsedited  13:45
Open / Comment
2023-05-09 21:58:18
የሐዘን መግለጫ

የአንደኛ ዓመት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪያችን የነበረው ተማሪ አበባው  ስንሻው መጸዳጃ ቤት ውስጥ ገብቶ  የመጸዳጃ ቤቱን  በር በመቆለፍ በራሱ ቀበቶ ራሱን አጥፍቶ በመገኘቱ ዩኒቨርሲቲያችን የተሰማዉን ጥልቅ ሐዘን ይገልፃል።

ተማሪው እዚህ አሳዛኝ ውሳኔ  ላይ እንዲደርስ ያበቁትን ጉዳዩች ተጨማሪ ማጣራት የሚያስፈልግ ቢሆንም ፈተና ከበደኝ በሚል ሲጨናነቅ እንደነበር መረጃዎች ያሳያሉ። ስለሆነም ለቤተሰቦቹ ፣ ለጓደኞቹና ለዩኒቨርስቲያችን ማህበረሰብ በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን!

ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT
5.7K viewsedited  18:58
Open / Comment
2023-05-09 17:41:22
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ 6ኛ እና 8 ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ቀናት ይፋ አደረገ።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የፈተና ዝግጅትና አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዲናኦል ጫላ የ 8ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 19 እና 20 እንዲሁም የ 6ኛ ክፍል ፈተና ሰኔ 26 እና 27 እንደሚሰጥ ተናግረዋል::


አያይዘውም ቢሮው ከተማ አቀፍ ፈተናዎቹን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመስጠት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያደርግ መቆየቱን የተናገሩ ሲሆን ትምህርት ቤቶች ተማሪዎቹን የበለጠ ማዘጋጀት እንዲችሉ ከከተማና ክፍለ ከተሞች ጋር በጋራ በመሆን የሞዴል ፈተናዎችን እንዲሰጡ አሳስበዋል ::


በ 2015 ዓ. ም 75,100 የ8ኛ እንዲሁም 75,078 የ 6ኛ ክፍል ተማሪዎች ከተማ አቀፍ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከስራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ያሳያል ::


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
5.4K viewsedited  14:41
Open / Comment
2023-05-04 13:49:46
#Tigray

በትግራይ ተቋርጦ የነበረው መደበኛ ትምህርት ከሠኞ ጀምሮ በተለያዩ ትምህርት ቤቶች ተጀምሯል።

ትምህርት የተጀመረው አዳዲስ አሰራሮችን  ተግባራዊ በማድረግ መሆኑን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ኪሮስ ጉዕሽ ለኢቢሲ በሰጡት ቃል ተናግረዋል።

ዶ/ር ኪሮስ ጉዕሽ  ምን አሉ ?

" ትምህርቱ ከሚያዚያ 24 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 7 ቀን 2015 ድረስ ለ2 ወር ተኩል በማካሄድ  የመጀመሪያው መንፈቅ ይጠናቀቃል። ይህም እንደ አንድ ወሰነ ትምህርት ጊዜ ይይዛል።

እንዲህ ያለው የትምህርት ዘዴ ወይም (Accerated Learning Program) ተማሪዎች እድሜያቸው መድረስ በሚገባቸው የትምህርት እርከን ላይ እስኪደርሱ በዓመት ሁለት ደረጃ ትምህርቶችን እንዲያልፉ ተደርጎ ተሰርቷል።

በዚህም አንድ ዓመት 4 የወሰነ ትምህርት ጊዜ በማድረግ ሁለት ደረጃ ትምህርት በአንድ ዓመት እንዲጨርሱ ይደረጋል። "

በሌላ በኩል ቢሮው ፥ በጦርነቱ ምክንያት ብዙ ጉዳት በመድረሱ የልዩ ፍላጎት የሚያስፈልጋቸው ተማሪዎች ቁጥራቸው  በከፍተኛ ሁኔታ እንደጨምር አሳውቋል።

የጉዳቱን መጠን በመረዳት የፌዴራል መንግስት፣ ትምህርት ሚኒስቴር ፣ ዓለም አቀፍ  የእርዳታ ድርጅቶች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት አስቸኳይ ድጋፍ  እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
1.3K viewsedited  10:49
Open / Comment
2023-05-04 11:52:22
ዓዲግራት ዩኒቨርስቲ ዳግም የመማር ማስተማር ስራው ለመጀመር የጥገና ስራዎችእየተሰሩ ይገኛል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
1.9K views08:52
Open / Comment
2023-05-04 11:38:06 በግቢው ጥበቃ የተመታችው ተማሪ በፍትህ ፋንታ ማስፈራሪያ እየደረሰባት እንደሚገኝ ገለጸች።

የእንጅባራ ዩኒቨርሲቲ የ2ኛ አመት Hotel and Tourism managment ተማሪ የሆነችው ኤደን ገብሩ በግቢው ተረኛ ጥበቃ በመመታቷ በደረሰባት ጉዳት ሆስፒታል ተኝታ እንደምትገኝ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በደረሰው ጥቆማ መሰረት ጉዳዩን ከተጎጂ፣ ከዓይን እማኞችና ከግቢው አካላት ለማጣራት ሞክረናል።

ተማሪ ኤደን ባነጋገርንበት ወቅት ጥቃት የደረሰባት በቀን 21 ዕለተ ቅዳሜ ጠዋት ላይ ከጓደኛዋ ጋር ቤተክርስቲያን ሄደው ሲመለሱ እንደሆነ ገልጻለች። መታወቂያ(ID) ባለመያዟ በር ላይ የሚቆጣጠሩ ጥበቃዎች አላስገባ እንዳሏት፤ እሷም እንደጠፋባትና በሚል ካርድ (በመመገቢያ ካርድ) ለመግባት መጠየቋን፤ በዚህም መከልከሏን ትናግራለች።

በር ላይ ከነበሩት ጥበቃዎች ሴት ጥበቃ እንደነበረችና እሷን እያዋራች በነበረችበት ሰዓት አንዱ ጥበቃ "ዞር በይ" በማለት ትከሻዋን በተደጋጋሚ ሲገፈትራት "አትገፍትረኝ" እንዳለችውና ከዚያ በኋላ በጥፊ እንደመታት፤ ከእንብርቷ በታች እንደረገጣት ትገልጻለች።

ከዚህ በኋላ ሌላኛው ዘበኛ "እንዴት ትነጋገሪያለሽ ቢመታሽስ አባትሽ አይደል" በማለት አባብሎ ወደ ግቢ እንዳስገባት፤ ከዚያም ጓደኞቿ ደግፈዋት ወደ ዶርም እንዳስገቧት ታስታውሳለች።

ጉዳዩን በግቢው ባለ ሴቶችና ህጻናት በማምራት ጉዳይዋን ብታማክርም ሰኞ ዕለት ማመልከቻ ይዛ እንድትመጣና አሁን መስራት እንደማይችሉ ይነግሯታል። እዛው ቢሮ እንዳለች እራሷን ስታ መውደቋን የምታስታውሰው ተማሪ ኤደን፥ በመጀመሪያ ወደ ግቢው ሆስፒታል ቀጥሎም በሪፈር ወደ ከተማው ሆስፒታል ተወስዳለች።

በሆስፒታልም X-ray እና UltraSound ተነስታ በማኅጸን አከባቢ ደም መቋጠሩንና ለሦስት ቀን ክትትል ተደርጎ መድኃኒቱ ካልበተነው ቀዶ ጥገና እንደሚደረግላት እንደተነገራት ታስታውሳለች። ሆኖም ሰኞ ዕለት "ውጤትሽ ጤናማ መሆንሽን ነው ሚያሳየው ውጪ" እንደተባለችና ህመሙ ግን እንዳልተሻላት ባነጋገርናት ወቅት ነግራናለች።

ተማሪ ኤደን፥ የምርመራ ውጤቱን ለቤተሰብ መላክ እንደምትፈልግና ውጤቱን እንዲሰጣት ብትጠይቅም ከግቢ አጽፋ ካልመጣች ውጤቱን መስጠት እንደማይችሉ ከሆስፒታሉ እንደተነገራት ተናግራለች።

ይህንን ያደረገው ጥበቃ ምንም አይነት ህጋዊ እርምጃ እንዳልተወሰደበት የሰማን ሲሆን ከዩኒቨርስቲው አስተዳደር በኩል ማጣራት አልቻልንም።

"እስካሁን ድረስ በሚገባ ድጋፍና ክትትል ሳይደረግልኝ ተኝቼ ነው ያለውት፤ የአልጋ ወጪ ብቻ ነው የተቻለልኝ ሌላውን ሁሉንም ወጪ ከራሴ ነው የከፈልኩት፤ ነገሮች እየተሸፋፈኑ እየታለፉ ነው፤ የሚመለከተውም አካል ምላሽ እንዲሰጠኝ እማጸናለሁ" ስትል በእንባ የታጀበ ተማጽኖዋን አቅርባለች።

አሁን ላይ ጉዳዩን ለምን ወደ ሚዲያ አወጣችሁ በሚል የተለያዩ ማስፈራሪያዎች እየደረሰባት እንደሆነ የገለጸችው ተማሪዋ ከየትኛው አካል እንደሆነ ገልጽ አላደረገችም። ከቀናት በኋላ የዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮች በሆስፒታል ተገኝተው እንደጠየቋት ቲክቫህ ሰምቷል።

የግቢው የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ዳይሬክቶሬት ምላሽ፦

"ለናንተ ልሰጥ የምችለው ምንም አይነት መረጃ የለኝም፤ ልክ እናንተ እንደሰማችሁት ነው እኔም የሰማውት፤ እጄ ላይ ምንም አይነት ማስረጃ የለም" የሚል አጭር ምላሽ አግኝተናል።

ከዚህ በተጨማሪ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ሌሎች የዩኒቨርስቲው አመራሮችን በስልክ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ስልክ ባለማንሳትና መረጃ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሊሳካ አልቻለም። በቀጣይ ዩኒቨርስቲው በጉዳዩ ላይ የሚሰጠው ምላሽ ካለ ተቀብለን የምናቀርብ ይሆናል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
1.9K views08:38
Open / Comment
2023-05-04 11:37:35
1.6K viewsedited  08:37
Open / Comment
2023-05-04 11:37:35
የትምህርት ሚኒስቴር የእንግሊዝኛ ቋንቋን በበጎ ፍቃደኝነት የማስተማር ፍላጎት ያላቸው ዜጎች የሚመዘገቡበት የመረጃ ፖርታል ይፋ አድርጓል፡፡

የከፍተኛ ትምህርት የመረጃ ፖርታሉ በእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት የሚታየውን የጥራት ጉድለት ለማስተካከል እንደሚያግዝ ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተናግረዋል፡፡

በእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት የጥራት ውስንነትን ለማስተካከል በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የበጎ ፍቃድ አገልግሎት እንዲሰጡም ሚኒስትሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

የትምህርት ሚኒስቴር ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በመተባበር ነጻ የእንግሊዝኛ ቋንቋ መማሪያ መተግበሪያ ማዘጋጀቱንም ሚኒስትሩ አስታውሰዋል።

በተጨማሪም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መምህራን እና ተመራማሪዎች በተቀናጀ መልኩ ግንኙነት የሚያደርጉበት ፖርታል ሥራ መጀመሩንም የኢዜአ ዘገባ ያሳያል፡፡

የእንግሊዝኛ ቋንቋ ትምህርት በኢትዮጵያ ከ70 አመት በላይ የማስተማሪያ ቋንቋ በመሆን እያገለገለ ይገኛል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
1.7K views08:37
Open / Comment