🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)

Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት) S
Logo of telegram channel nationalexamsresult — STUDENTS NEWS CHANNEL (የተማሪዎች ዜና መስኮት)
Channel address: @nationalexamsresult
Categories: Education
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 41.40K
Description from channel

የተማሪ እና ተማሪ ነክ መረጃዎች ይቀርቡበታል፡

Ratings & Reviews

2.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

1

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 14

2023-04-22 21:22:32
ዲላ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተናን ለመተግበር የሚያስችል የ"ኦንላይን" ፈተና አስተዳደር ስርዓት አበለጽጓል።

ስርዓቱ በዩኒቨርሲቲው የኮምፒውተር ሳይንስ መምህራን መበልጸጉ ተገልጿል።

የ"ኦንላይን" ፈተና አሰተዳደር ስርአቱ ከበላይ አመራሮች ጀምሮ የኮሌጅ ዲኖች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ መምህራን እንዲሁም ተማሪዎች በተፈቀደላቸው ልክ እንዲከውኑበት ተደርጎ የበለጸገ ነው ተብሏል። #ዲዩ

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
1.9K viewsedited  18:22
Open / Comment
2023-04-22 15:10:58
One Young World Summit 2023 in Belfast (Fully Funded)

The OYW Summit will bring 2000+ Participant's from all countries for a 4 Day Summit (2-5 Oct 2023)

Open to anyone. No IELTS. No Fee

The Program Covers Airfare Tickets, Accommodation, Health, Visa Fee, Meals and everything.

Visit: https://opportunitiescorners.com/one-young-world-summit/

Deadline: 30th April 2023

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
3.1K viewsedited  12:10
Open / Comment
2023-04-22 15:10:58 #እንድታውቁት

የኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት ለማስቀጠል በዝግጅት ላይ እንደሆነ ገልጿል።

በመሆኑም በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ #የማይገኙ ሁሉም የዲግሪ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን፣ ክረምት) እንዲሁም የማስተርስ (መደበኛ፣ ኤክስቴንሽን ፣ ክረምት) ተማሪዎች ከዚህ በታች ባለው ሊንክ እንዲመዘገቡ ጥሪ ቀርቧል።

ሊንክ ፦ http://196.190.28.50

ምዝገባው የሚያበቃበት ቀን ሚያዚያ 18 ቀን 2015 ዓ/ም መሆኑን ተቋሙ አሳውቋል።

ለበለጠ መረጃ ደግሞ ዘውትር በየስራ ሰአት በሚከተሉት ቁጥሮች መወደወል ይቻላል ፦ 0914485592 / 0921990158

ከኣክሱም ዩኒቨርሲቲ በተጨማሪ #የራያ_ዩኒቨርሲቲም በጦርነት የተቋረጠውን መደበኛ ትምህርት ለማስቀጠል እየሰራ ይገኛል።

በዚህም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት በራያ ዩኒቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩና ወደ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው የመማር እድል ያላገኙ ተማሪዎች ከ09/08/2015 ዓ/ም እስከ 13/08/2015 ዓ/ም ባሉ የስራ ቀናት እንዲመዘገቡ ጥሪ አቅርቧል።

ተማሪዎች የሚመዘገቡት ለዩኒቨርስቲው ረጅስትራር እየደሉ ሲሆን የስልክ ቁጥሮቹ 0970140000፣ 0970240000 ፣ 0970230000 ናቸው። ተማሪዎች ዘውትር በስራ ሰዓት ብቻ እንዲደውሉ ጥሪ ቀርቧል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
2.8K viewsedited  12:10
Open / Comment
2023-04-22 15:10:58
2.3K views12:10
Open / Comment
2023-04-22 11:38:17
A+ Tutorial Class

የመጀመሪያ አመት የ ዩኒቨርሲቲ ና የኮሌጅ ተማሪዎች በአዲሱ ፍኖተ ካርታ መሰረት የሚወስዱትን freshman course ለመረዳት ምቹ ÷ ግልፅ የሆኑ ኖቶችን እና ማብራሪያዎችን ከ ምስል እና ከ PDF ፋይል ጋር አቀናጅቶ በማስተማር ብዙ ሺህ ተማሪዎች ለከፍተኛ ውጤት እንዲበቁ አስተዋዕፆ ያደረገው ÷

በሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከፍተኛ ውጤት  በማምጣት የከፍተኛ ውጤት ባለቤት በመሆን ወደሚፈልጉት ዲፓርትመንት እንዲቀላቀሉ በማድረግ ከፍተኛ ተወዳጅነትን እና ተከታይነትን ያተረፈው A+ Tutorial Class ለዘንድሮ ለ 2015 አዲስ ገቢ የ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በማስተማር ለ ፈተና በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የበኩሉን አስተዋዕፆ በመወጣት ላይ ይገኛል።

ከላይ ለናሙና የቀረቡት ፎቶዎች በ ዘንድሮ በ A+ Tutorial Class እየተሰጠ ያለውን የ freshman course ቲቶርያል በ Natural Science ፤ በ Social Science እንዲሁም በ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የተመደቡ ተማሪዎች ሲከታተሉ የሚያሳይ ነው።

ይመዝገቡ ወደ ሚፈልጉት ዲፓርትመንት ለመቀላቀል የሚጠብቅዎትን ትግል ያቃሉ።

ለመመዝገብ
@AplusTutorialbot

ለጥያቄ ና ሀሳብ
@ucan_scorebot

ለበለጠ ከአምና ከ 2014 ተማሪዎች ጋ በነበረን ቆይታ ከተሰጡ ብዙ ምስክርነቶች መካከል ለናሙና የቀረቡትን ምስክርነቶች ገብታችሁ ማየት ትችላላችሁ

https://t.me/+b1zKh1uFuytlZWI0

ስኬትዎ ከA+ ጋር የተረጋገጠ ነው!
Your Sucess is guaranteed with A+ Tutorial Class!

A+ Tutorial Class.
3.3K views08:38
Open / Comment
2023-04-21 06:15:57
የወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ ተማሪዎች ቅሬታ

በወላይታ ሶዶ ዩንቨርሲቲ ዳውሮ ታርጫ ካምፓስ መብራት ከጠፋ #40 አካባቢ ማለፉን ተከትሎ በግቢው ውስጥ የሚገኙ ከ1500 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ባለፉት ቀናት ተደጋጋሚ ቅሬታዎችን ሲያሰሙ ቆይተዋል። በርካታ ተማሪዎች ጨለማ ላይ እንደሚገኙና ትምህርታቸውን ለመከታተልም እያዳገታቸው እንደሆነ ለATC ሲገልፁ ሰንብተዋል።

ይህ የመብራት ለበርካታ ሳምንታት መቋረጥ ያስመረራቸው የግቢው ተማሪዎች በትላንትናው ዕለት ሻንጣቸውን በመያዝ ከግቢ ለመውጣት የሞከሩ ቢሆንም የፌደራል የፀጥታ ኃይሎች ከግቢ እንዳይወጡ እይዳደረጓቸው ገልፀውልናል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአንድ ወር በላይ በዞኑ ተቋርጦ የነበረው የመብራት አገልግሎት ከሰዓታት በኋላ እንደሚለቀቅ የዞኑ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ገልጿል።

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
4.9K views03:15
Open / Comment
2023-04-21 06:13:35 የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎች ዝግጁ እንዲሆኑ አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው መሆኑን የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ገለጹ

የትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ዓመት የዩኒቨርስቲ መውጫ ፈተና እንደሚሰጥ ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

መውጫ ፈተናው ተማሪዎች በሰለጠኑባቸው የሙያ ዘርፎች ብቁ መሆናቸውን ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ፡፡

የመውጫ ፈተና በኦንላይን ለሁሉም የመንግስት ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የሚሰጥ ሲሆን ኢዜአ ያነጋገራቸው የመንግስት ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንቶች ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በመነጋገር መውጫ ፈተናውን ለመስጠት ተዘጋጅተዋል፡፡

የጅማ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ጀማል አባፊጣ መውጫ ፈተና ተማሪዎች በዩኒቨርስቲ ቆይታቸው የሚጠቀሙባቸውን እውቀት ክህሎትና አመለካከት በብቃት መያዛቸውን መለኪያ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ይህም ብቻ ሳይሆን ዩኒቨርስቲዎች በትምህርት አሰጣጥ ላይ ያሉበትን ሁኔታ በማሳየት የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሚናው የጎላ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡

የዩኒቨርስቲው ማህበረሰብ የመውጫ ፈተናውን በሚመለከት የግንዛቤ ማስጨበጫ መሰጠቱንና አስፈላጊውን ግብዓት የማሟላት ስራ እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ከዚህ ጎን ለጎንም ተፈታኞችን በእውቀትና በስነልቦና የማዘጋጀት ስራ መሰራቱንም ጠቅሰዋል፡፡

የባህርዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ፍሬው ተገኝ በበኩላቸው የመውጫ ፈተና ውጤት ፍትሀዊነትን የሚመልስ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

የመውጫ ፈተናው የመጀመሪያው እንደመሆኑ መጠን ለተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫና ድጋፍ ለሚፈልጉ ተማሪዎች ድጋፍ የማድረግ ስራ እየተሰራ ስለመሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፈተናው የሚሰጥባቸውን የትኩረት መስኮች በመለየት የማጠናከሪያ ፕሮግራም እየተሰጠ ነው ያሉት ደግሞ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ዶክተር ዳምጠው ደርዛ ናቸው፡፡

ጎን ለጎንም ለሴቶችና ልዩ ፍላጎት ላላቸው ተማሪዎች በልዩ ሁኔታ ተኩረት ተሰጥቶ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል ፕሬዚዳንቱ፡፡

የከፍተኛ ትምህርት አገራዊ ቅድመ ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና በአግባቡ ለመምራትና ለማስተዳደር የተዘጋጀው የፈተና ማስፈጸሚያ መመሪያ ባለፈው ዓመት ነሀሴ ወር ላይ መጽደቁ ይታወሳል፡፡

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
4.4K viewsedited  03:13
Open / Comment
2023-04-21 05:52:31
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

መልካም በዓል


Team : @NATIONALEXAMSRESULT
4.0K viewsedited  02:52
Open / Comment
2023-04-20 15:55:39 አራት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን በፌስቡክ ማንነቱን ቀይሮ በመተዋወቅ ‘‘ካናዳ እና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’ በማለት ጾታዊ ግንኙነት እንዲፈጽሙ አድርጓል የተባለው ግለሰብ በጽኑ እስራትና በገንዘብ ተቀጣ።

ግለሰቡ ከግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ እና 20 ግራም ወርቅ ተቀብሎ የማታለል ወንጀል ፈጽሟል ተብሎ ነው በጽኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጣ የተወሰነው። የቅጣት ውሳኔውን የወሰነው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ 2ኛ አርቲዲ ወንጀል ችሎት ሲሆን÷ተከሳሹ ታዲዮስ ዘላለም በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 06 ነዋሪ ነው።

ተማሪዎችን በማህበራዊ ትስስር ገጽ “ናቲ መላኩ” ብሎ ማንነቱን ቀይሮ በካናዳ ነዋሪ በመምሰል ከተዋወቃቸው በኋላ ‘’ካናዳና እንግሊዝ እወስዳችኋለው’’ ብሎ የማታለል ተግባር መፈጸሙ በክሱ ተመላክቷል። ከዚህም በኋላ ተከሳሹ ከካናዳ ወደ አዲስ አበባ እንደመጣ በማስመሰል በግንቦትና በሰኔ ወር 2014 ዓ.ም በተለያዩ ቀናቶች ለ4 የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የግል ተበዳዮች ስልክ ይደውላል፡፡ በዚህም'' ከእንግሊዝ ኤምባሲ ጉዳይ የሚፈጽምላችሁ ሰው ይመጣል፤ አሻራ የሚወሰደው ከዘር ፈሳሽ እና ከወርቅ ስለሆነ አልጋ ይዛችሁ ጠብቁ በማለት'' የግል ተበዳዮች በተለያየ ቀናቶች በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 13 አልጋ ይዘው እንዲጠብቁ ማድረጉ በክሱ ተጠቅሷል።

አልጋ እንዲይዙ ካደረገ በኋላ ማንነቱን ቀይሮ ወደ አልጋ ቤት በመሄድ የግብረስጋ ግንኙነት እንዲፈጽሙ ማድረጉም በክሱ ተመላክቷል።

በተጨማሪም ተከሳሹ ከግል ተበዳይ ተማሪዎች ከእያንዳንዳቸው የተለያየ መጠን ያለው በአጠቃላይ 20 ነጥብ 7 ግራም ወርቅ ለአሻራ ምርመራ ያስፈልጋል ብሎ መውሰዱ በክሱ ተገልጿል፡፡ ለጉዳይ ማስፈጸሚያ በሚል ከእያንዳንዳቸው ግማሽ ሚሊየን ብር በላይ ገንዘብ መቀበሉም በክሱ ተዘርዝሯል።

ተከሳሹ ከግል ተበዳዮች መካከል ከአንደኛዋ ተማሪ ጉዳይ ለማስፈጸም "አይፎን "ሞባይል ስልክ ያስፈልጋል በማለት እንድታመጣ በማዘዝ የስልክ ቀፎውን ለመቀበል በቀጠራት ዕለት ፖሊስ በደረሰው ጥቆማ በኦፕሬሽን ክትትል በቁጥጥር ስር መዋሉ  በክሱ ተመላክቷል። በዚህም ተከሳሹ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 692/1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ በመተላለፍ በማታለል ወንጀል ተደራራቢ አራት ክሶች ቀርቦበታል።

ተከሳሹ ክሱ ከደረሰውና በችሎት በንባብ ከተሰማ በኋላ ወንጀሉን አልፈጸምኩም ሲል የዕምነት ክህደት ቃሉን ሰጥቷል። የፍትህ ሚኒስቴር የቦሌ ምድብ ዓቃቤ ሕግ ለወንጀሉ መፈጸም ያስረዳሉ ያላቸውን የግል ተበዳዮችን ጨምሮ 6 ምስክሮችን በችሎት አቅርቦ የምስክርነት ቃላቸውን አሰምቷል።

ፍርድ ቤቱ የምስክር ቃል መርምሮ ተከሳሹ ወንጀሉን መፈጸሙ በዐቃቤ ሕግ ምስክር ቃል ማረጋገጡን በመግለጽ ተከሳሹ በተከሰሰበት አንቀጽ እንዲከላከል ብይን ተሰጥቶ ነበር። ይሁንና ተከሳሹ የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን መከላከል ባለመቻሉ በመጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም በዋለው ችሎት በተከሰሰበት በአራት ክሶች በአንቀጽ 692 (1) ስር የጥፋተኝነት ፍርድ ተላልፎበታል።

ተከሳሹ ለመከላከያ ሰራዊት ድጋፍ ማድረጉን ለህዳሴ ግድብ የቦንድ ግዢ መፈጸሙን እንዲሁም ለማህበራዊ በጎ አድራጎት  ያበረከተውን አስተዋጾን የሚገልጽ   ከቦሌ ክ/ከ ወረዳ 13  ጽዳት አስተዳደርና ከዚሁ ወረዳ ከሴቶችና ሕጻናት ቢሮ የተሰጠውን ማስረጃ ጨምሮ  አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት አቅርቦ በፍርድ ቤቱ ተይዞለታል።

በዐቃቤ ሕግ በኩል ግን የቅጣት ማክበጃ አስተያየት አለመቅረቡን የችሎቱ ዳኛ ገልጸዋል።

በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 2/2006 መሰረት በደረጃ ስድስት በዕርከን 25 መነሻ በ7 ዓመት ጽኑ እስራት እንዲቀጣ የተወሰነ ሲሆን÷በዕርከን 3 መሰረት ደግሞ በ3 ሺህ ብር የገንዘብ እንዲቀጣ ተወስኗል። ቅጣቱን የአዲስ አበባ  ማረሚያ ቤት እንዲያስፈጽም የታዘዘ ሲሆን÷የቅጣት ውሳኔ ሲወሰን የግል ተበዳይ ከሆኑት ተማሪዎች መካከል ሁለቱ በችሎት ተገኝተው ቅጣቱን ተከታትለዋል።(በታሪክ አዱኛ)

የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
2.5K viewsedited  12:55
Open / Comment
2023-04-20 10:54:30
#RayaUniversity

በራያ ዩንቨርሲቲ መደበኛ ትምህርት ስትከታተሉ ቆይታቹህ በተፈጠረው ጦርነት ምክንያት ትምህርታችሁን ላቋረጣቹህ ተማሪዎች በሙሉ፣

በራያ ዩንቨርሲቲ በመደበኛ ፕሮግራም ከ2ኛ እስከ 5ኛ ዓመት ትምህርታችሁን ስትከታተሉ የነበራችሁና ወደ ሌሎች ዩንቨርሲቲዎች ተመድባቹህ የመማር ዕድል #ያላገኛቹህ ተማሪዎች በስራ ሰዓት ብቻ ከ09-13/2015 ድረስ በሚከተሉት ስልክ ቁጥሮች እየደወላቹህ ተመዝገቡ።

# Raya University registration
የራያ ዩኒቨርስቲ ምዝገባ ከ 09-13/08/2015
via 1.0970140000
2.0970240000
3.0970230000
N.b-በስራ ቀንና በስራ ሰዓት ብቻ

ዩንቨርሲቲው ሙሉ ዝግጅቱን ሲያጠናቅቅ የግቢ መግቢያ ቀንን በመገናኛ ብዙሃን እንደሚያሳውቅ ገልጿል።


የተጣሩ ተማሪ ነክ መረጃዎችን ለማግኘት ቻናላችንን ይቀላቀሉን
@NATIONALEXAMSRESULT

Click here for advertisement
@studentsnewsadv35bot
3.4K viewsedited  07:54
Open / Comment