🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ

Channel address: @bewketuseyoum19
Categories: Courses & guides
Language: English
Subscribers: 133.01K
Description from channel

➲የበእውቀቱ ስዩም ፈገግታም እውቀትም የሚሰጡ ወጎች ፣ ግጥምች እና የተለያዩ ፀሀፊዎች የስነጽሑፍ ስራዎች የሚቀርብበት ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
@bewketuseyoum19
Buy ads: https://telega.io/c/bewketuseyoum19
For your comment,feedback and promotion @Bewketuseyoum2bot
Thank you!

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 17

2023-04-13 20:40:13 የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........


(ሜሪ ፈለቀ)

ክፍል 19

እንዲህ ነው የሚመስለኝ :- የራሴን ህይወት ራሴው ኖሬው እና ሌላ ሰው ሆኜ ደግሞ ከውጪ ሳየው!! ራሴን ሌላ ሰው ሆኜ ባየው ምን አይነት ሰው ነኝ ብሎ አስቦ የሚያውቅ ሰው ይኖራል? እድሉ ተሰጥቶትስ ራሱን ከውጪ ቢያየው ስንት ሰው ራሱን ይወደዋል? ወይስ ይፀየፈዋል?

እንግዲህ መታደል ይሁን መረገም እኔ የደረሰኝ ይህ እጣ ነው!! እንደ ሌላ ሰው ከውጪ ያየኋትን የድሮዋን ሜላት ድጋሚ መኖር ወይም ሌላ ሜላትን መፍጠር ደግሞ ከፊቴ ያሉ ምርጫዎች ናቸው። ሁለቱም አስፈሪ ምርጫ ነው!!!

በደም በተለወሰ ልብሴ ደሙ እጅና ፊቴ ላይ ደርቆ የሆስፒታሉ መጠበቂያ ቦታ ለሰዓታት ከአንዱ ቦታ ወደሌላው እንደፌንጣ እየዘለልኩ ነው ይሄን የማስበው። ስንት ሰዓት እንደጠበቅን ከማላውቀው ጊዜ በኋላ ከዛ ውጥንቅጥ ቦታ ይዞን የመጣው የጎንጥ ወዳጅ ወንበሩ ላይ ከነበረው ሰውነት በግማሽ ያነሰ መስሎ ተኮራምቶ እንደተቀመጠ

«መታጠቢያ እኮ አለ ቢያንስ ደሙን ከሰውነትሽ ታጠቢ!! ወይ መቀየሪያ ልብስ ላምጣልሽ?» ያለኝ እሱም እንደእኔ ሰውነቱ በደም መቅለሙን ሳያውቀው ይሆን እንጃ!! <አንተምኮ ደም ብቻ ነህ!> ማለት እፈልጋለሁ ግን አፌ ተለጉሟል። አውልቄ የጎንጥን ደም ለማስቆም ቁስሉ ላይ ይዤው የነበረውን ሹራቤን ይዞት ነው የተቀመጠው። - የኪዳን መልዕክት!! ዘልዬ ተነስቼ ሹራቡን ስወስድበት ብርግግ ብሎ አፈጠጠብኝ!!

«ሜል ይቅርታ እሺ!! ብዙ የምፅፍበት ጊዜ እና ሁኔታ ላይ አይደለሁም!! ማስታወስ እንደማትችዪ ሲያወሩ ሰምቻለሁ። ነገሮችን ስገጣጥማቸው ገባኝ!! እመቤትን እመኛት!! ያለችሽ ብቸኛ ጓደኛ እሷ ብቻ ናት!! ሌላው እኔ ማን እንደሆነች ብዙ ያልገባኝ አምነሽ ቪዲዮዎቹን ኮፒ ያስቀመጥሽባት ሴት አሁን ከእነርሱ ጋር ናት!! በቢዲዮዎቹ እየተደራደረች ነው!! እንዳታምኛት!! ታውቂ የለ እወድሽ የለ?»

«ይህቺ ከንቱ!» አልኩኝ ሳላስበው!! ወትሮም ጓደኛዬ አይደለችም!! ጥቅም ነው ያገናኘን!! እኔ ለጥቅሟ የምደምርላት ነገር እንደሌለ ባወቀች ቅፅበት ልትቀብራቸው ጉድጓድ ስትምስ የኖረችባቸው ሰዎች ጋር ሌላ የጥቅም ወጥመድ የዘረጋችበት ፍጥነት ……. ድሮም ትርፍ ካገኘችበት የገዛ ባሏን ከመሸጥ የማትመለስ ነጋዴ መሆኗን አውቃለሁ። የከንቲባው ሚስት ናት!! ባሏ ከንቲባ ከመሆኑ በፊት ከደሳለኝ (ኪዳንን ያገተው ሰውዬ) ጋር ወዳጃሞች ነበሩ!! ለአንድ ቦታ ለመመረጥ ፉክክር እስከጀመሩባት ጊዜ አንዳቸው ከሌላቸው ቤት የማይጠፉ፣ ልጆቻቸው እንደእህትና ወንድም የተቋለፉ ፣ ሚስቶቻቸው ከፀጉር ቤት እስከ ትልልቅ የህዝብ መድረክ ተቆላልፈው የሚተያዩ ዓይነት ነበሩ። ከንቲባው ሞተሩ ሚስቱ ናት እንደፈለገች በቀን ሙዷ የምታሾረው እንጂ የዋህ ቢጤ ነው። ደሳለኝ በገዛ ፍቃዱ ከውድድሩ ራሱን እንዲያገል ያን መረጃ ከእኔ ጋር በልዋጭ ጥቅም ተደራድራ ነው!! ተማምነን አይደለም የጠላቴ ጠላት በሚለው ተወዳጅተን እንጂ!! እከኪልኝ ልከክልሽ ተባብለን ነገር ……. እኔ አደጋ ላይ ብወድቅ እሷጋ ያለው ቅጂ ማስያዣ እንዲሆን ፤ እሷ አደጋ ላይ ብትወድቅ እኔ ጋር ያለው ቅጂ መገበያያ እንዲሆን ነበር ውላችን!! ድንገት በአንድ ቀን ጀንበር ያለድካም የተገነባ መተማመንም አልነበረም!! ከአንዲት 10 ሺህ ህዝብ ከሚኖርባት መንደር ወጥቼ ስልጣኑና አቅሙ አለን ከሚሉት ወንበዴዎች ጋር ለመግባት ለመውጣትስ የተጓዝኩት ጉዞ ቢሆን በቀላል ድካምና ላብ የተገነባ መች ነበር?

«የአቶ ጎንጥ ቤተሰቦች?»

ዘልዬ ተነሳሁ!! ዶክተሩ ከማውራቱ በፊት ነገረ አካላቴን በሀዘኔታ እያየ ነው ቀዶ ጥገናውን በስኬት መጨረሱን የነገረን።

«እስኪነቃ ድረስ እቤት ሄደሽ ተጣጥበሽ ልብስሽን ቀይረሽ መምጣት ትችያለሽ!!» አለኝ የጎንጥ ወዳጅ!! አልሄድኩም!! ተናኜጋ ደውዬ የምቀይረው ልብስ እንድታመጣልኝ አደረግኩ። ስልኩን ስዘጋ ተናኜ መርሳቴን አስታክካ የተቀበለችውን ደሞዝ ድጋሚ እንደተቀበለችኝ አስታውሼ ፈገግ አልኩ። የጎንጥን መመታት ስነግራት ያዙኝ ልቀቁኝ ማለቷስ? የአባቷን ለቅሶ የተረዳች አስመስላ አረፈችው። ልብሴን ቀያይሬ እንድትረጋጋ ላሳያት የተኛበት ክፍል ይዣት ብገባ ተኝቶ ስታየው ያን ለቅሶዋን አመጣችው። የልብሷን አንገትጌ በእጇ ጨምድዳ ይዛ ወደአፏ አስገብታ ንክስ አድርጋ…… <ህእእ > እያለች ሳጎን ወደ ውስጥ እየሳበች ተነፋረቀች።

«ምን ልሁን ነው ምትይ?» ሲል ነው መንቃቱን ያየነው። ይሄኔ ግራ የገባው ስሜት ተሰማኝ። የሆነኛው ልቤ (የሁለት ወሯ ሜላት ልብ ይመስለኛል) ስለነቃልኝ መፈንጠዝ ፣ አጠገቡ ሄጄ መነካካት ያምረዋል። የሆነኛው ልቤ (የድሮዋ ሜላት ልብ ይመስለኛል) ቆጠብ ማለት ፣ ኮስተር ማለት ያምረዋል። አጠገቡ ደረስኩ ግን እጁን ሊይዘው የተዘረጋ እጄ መንገድ እንደሳተ ነገር የአልጋውን ጫፍ ጨበጠ። ቅድም ሁለት ምርጫ አለኝ አላልኳችሁም? ወይ አሮጌዋን መሆን ወይ አዲስ መሆን? ሁለቱንም መሆን እንደማልችል እዚህ ጋር ገባኝ!! ቢያንስ በጎንጥ ጉዳይ!! ልቤ እና ሰውነቴ እንዳልተስማሙ ገብቶታል መሰለኝ ተናኜም ወዳጁም እግራቸው እንደወጣ ጠብቆ

«ተቀይመሽኝ ነው እንዴ?» ሲለኝ እስካሁን ስለማንነቱ፣ ስለዋሸኝ ዘበኝነቱ …… ተያያዥ ነገር ጭራሽ አለማሰቤ ገረመኝ። እዛ መኪናው ጋር ራሱን ከፊቴ አድርጎ የእኔን ሞት የተጋፈጠልኝ ሰዓት መቀየሜን ተውኩት? እዛጋ የበደለኝን አጣፋሁት?

«ቅያሜ አይደለም ያለኝ ጥያቄ ነው» አልኩት። ፈገግ ብሎ <ጠይቂኝ> እንደማለት በእጁ ወዲህ በይው ዓይነት ምልክት ሰራ። ወንበሩን ስቤ ከፊቱ እየተቀመጥኩ። <እዝህችው ቆመን 19 መቶ ብዬ እንዳወጋሽ አይደለማ ሀሳብሽ?> ብሎ የጮኸብኝ ትዝ ብሎኝ

«ገና ከመንቃትህ 19 መቶ ዓመተምህረት ብለህ ልታወጋኝ አይደለምኣ ሀሳብህ? (ፈገግ አለ) አንተ ጥለኸኝ የመጥፋት ሀሳቡ ከሌለህ በቀር እኔ የትም አልሄድም ያንተ እና የእኔ ጉዳይ ይደርሳል። ኪዳንን ጭረት ሳይነካው ዛሬውኑ ከዛ ቤት እንዲወጣልኝ ማድረግ አለብኝ።» አልኩት።

**

ልጅነቴ አጎቴ እንዳለው በጀግንነት እና ጀብድ ብቻ የተሞላ አልነበረም። ያ እነሱን ሆነው ሲያዩት የገባቻቸው ሜላት ናት። አባቴ የሞተበት ቦታ እየሄድኩ ሬሳው የነበረበት ቦታ ተቀምጬ በለቅሶ የምደነዝዝባቸውን የትዬለሌ ሰዓታት እሱ አያውቅም!! እናቴን የደፈራት ሰውዬ ፊት ለዓመታት በህልሜ እኔኑ ሲደፍረኝ እያየሁ በላብ ተጠምቄ ስንቀጠቀጥ የነጉትን ቁጥር አልባ ለሊቶች እሱ አያውቅም። ከሞቱ በፊት የነበረው የአባቴ ፊት ጠፍቶብኝ አባቴን ሳስብ የማስታውሰው የዛን ቀን ያየሁትን ፊቱን እየሆነብኝ ተሰቃይቼ ፎቶውን አቅፌ ማደሬን አያውቅም!! እናቴ ተመልሳ ትመጣ ይሆናል ብዬ ስንት ቀን እንደጠበቅኩ አያውቅም። አባቴን የገደሉብኝን ሰዎች ኮቲያቸውን ልኬት ሳይቀር በጭንቅላቴ ውስጥ ስዬ እንዳስቀመጥኩ አያውቅም!! ብዙ አያውቅም !! ብዙውን አልተናገርኩም!!

የማይቆጠር ጊዜ ቀዬውን ጥዬ ልሄድ አስቤ አውቃለሁ። አንድ ቀን ኪዳን ከትምህርት ቤት ሲመጣ እኔ እቤት አልነበርኩም!! እያለቀሰ ስሜን እየተጣራ ሲፈልገኝ አገኘሁት «ምን ያስለቅስሃል? ማን መታህ?» ነበር እንዳየሁት ያልኩት
«እ እ….
181 viewsAbela, 17:40
Open / Comment
2023-04-13 20:08:52 Are you single
627 viewsMerry G, 17:08
Open / Comment
2023-04-13 20:08:34
1, ዴርቶ ጋዳ
2, ዮራቶራድ
3, ራማቶሓራ
4, ዣንቶዣራ
5, ገመና
6, እመጓ
7, ካፖርቱ
8, የበደል ካሳ- በአጥናፍ ሰገድ ይልማ
9, ብርቅርቅታ
9, ፍቅር እስከ መቃብር
10, እሳት ወይ አበባ
11, አሌክስ አብርሀም
12, መግባት እና መውጣት
13, የተቆለፈበት ቁልፍ----redkey
14, በደል-------bedel
16, ኦሮማይ ደራሲ በአሉ ግርማ
17, ፍሬ አልባ በለሶች----rie Alba Belsoch
18, ከአድማስ ባሻገር ----በአሉ ግርማ
19, የገብረ ክርስቶስ ደስታ ግጥሞች
20, የቡርቃ ዝምታ
21, ስብሀት ለአምላክ
22,ዛሬ እንኩዋን እንሳቅ
23, አልወለድም ደራሲ አቤ ጉበኛ
24, ውዴ ስትናፍቀኝ
25, የሳቅ ምንጭ ደራሲ ሰለሞን
26, የእንስሳት እድር
27, መደመር
28, ስንክሳሬ
29, ለአሸናፊነት መገዛት ------victory
30, ትግላችን በኮ/መንግስቱ ሀ/ማርያም
31, ንቡት
32, አገቱና
34, አጤ ቴድሮስ
35, አሉላ አባ ነጋ
36, በቀለኛው ሰላይ
37, ጎረቤት ፈልጌ ነበር
38, ባሌ በ50 ብር ሸጠኝ
39, የሀውልቱ ስር ቁማርተኞች
40, መልስ አዳኝና ሌሎች
41, ሊዮኔ
42, ሌሎች አለማት
43, የቁራ ጩኸት
44, አርማጌዶን
45, ከጻረ ሞት ትንቅንቅ
46, መጽሀፈ ሄኖክ
47, የልምዣት ደራሲ አዲስ አለማየው
48, የዳቪንቼ ኮድ
49, የሼህ ሁሴን ጅብሪል ትንቢት
50, አንገረ ፈላስፋ (የፈላስፎች ንግግር)

የቱን መፅሀፍ ማንበብ ይፈልጋሉ የሚፈልጉት መፅሀፍ በመንካት ያንብቡ መልካም ንባብ
ይቀላቀሉን
484 viewsMerry G, 17:08
Open / Comment
2023-04-13 19:55:10 በሩን አልፈን እንደወጣን የቅድሟ ሴት ተቀበለችን። ስመጣ ያሰሩልኝን ጨርቅ ይዛ ስትቀርበኝ የያዘኝን እጁን ለቅቄ በጥያቄ አየሁት!! የታከትኩት መሰለ እና በቁጣ ጮኸ « እየገባሽ አይደለም አንቺን መምረጤ? ከዚህ በላይ ምን ባደርግ ነው የምታምኝኝ በይ? ያለፈውን ካላወቅኩ ነው? አንድም ሳይቀር አወጋሻለሁ! እዝህችው ቆመን 19 መቶ ብዬ እንዳወጋሽ አይደለማ ሀሳብሽ?» ቅድም ሴትየዋ ላይ እንደጮኸው ነው የጮኸው!! ጨርቁን እንድትሰጠው ለልጅቷ እጁን ሲዘረጋ ልጅቷ እንደማቅማማት አለች። ጮክ ብሎ ሲያፈጥባት የመወርወር ያህል እጁ ላይ ጣለችው። ከሁኔታዋ ከዚህ በፊት የሚተዋወቁ የምትፈራው ሰው መሆኑ ያስታውቃል። ምናልባት አለቃዋ ነበር? ዛሬማ የሆነ ፊልም ገፀ ባህሪ ሆኛለሁ።

ከሴትየዋ እጅ ተቀብሎ እሱ እያሰረልኝ እንደዛ እንዳልጮኸ ልስልስ ብሎ ነገር «መግቢያ መውጫቸውን እያየሽ እንድትሄጂ በጀ አይሉሽም!! ለዛሬ የምልሽን እሽ በይ በሞቴ?» አለ። ማደንዠዣ እንደወጉት በሽተኛ ፍዝዝ ድንግዝ አልኩ። ጨርቁን ካሰረልኝ በኋላ እጄን አጥብቆ ይዞ መራመድ ጀመረ። የምረግጠው ምን እንደሆነ ሳላውቅ እግሬን እያነሳሁ ተከተልኩት። መኪና ውስጥ ገባን!! ባላይም መኪናው ውስጥ ከእኔና ከእርሱ በተጨማሪ ያቺ እንደጥላ የምታጅበኝ ሴት እና ሹፌር እንዳሉ አውቂያለሁ። እኔእና እሱ መጓዝ ጀምረን የያዘኝ እጁ መያዝ ብቻ ሳይሆን መዳበስ ነገር ያደርገኛል። ልቤ የምን አጃቢ ናት አብራ የምትቀልጠው? ትንፋሹ እንዳልተረጋጋ ያስታውቅበታል። አካሉም ይቅበጠበጣል። ከእርሱ ሁኔታ በመነሳት አሁንም እርግጠኛ የሆነ ማምለጥ አለማምለጤን ጠረጠርኩ። ቆይ እራሱ የሆነ ቦታ አግቶ ይዞኝ እየሄደ ቢሆንስ? እሱንስ እንዴት አመንኩት?

«ሴትየዋ ማናት? ምንህ ናት?» አልኩት ከዛ ሁሉ አናቴን ከወጠረው ጥያቄ ይሄን ለምን እንዳስቀደምኩ አላውቅም!! በረዥሙ ተንፍሶ

«የልጄ እናት ናት!! ምሽቴ ነበረች» አላለኝም? ከዚህ በላይ ከእውነታ የራቀ ቀን አለ እሺ?
«እ?» የምትለዋ ፊደል ከየትኛው ቃል አምልጣ በአፌ እንደሾለከች አላውቅም!! ብቻ ለምሳሌ <እንደ> ከሚለው ቃል ቢሆን ተጣልተው የፈረጠጠችው …… <ን> ን እና <ደ>ን ትርጉም አልባ አድርጋ ጥላቸው ብቻዋን ስትፈረጥጥ …… ተንደርድራ አምልጣ መሆኑ የሚያስታውቀው አፌ ፊደሏን ሊያስወጣ እንደተበረገደ አልተከደነም!!

«ባሏ ነው!!» አለ አክሎ። ሰውየውን መሆኑ ገባኝ ግን ጭንቅላቴ ውስጥ ሀሳቦቹ ተጠላለፉ ነገር። የሰውየው የአሁን ሚስት የጎንጥ የድሮ ሚስት የልጁ እናት! ከዛ ግን ዛሬም ውሉን ያልጨበጥኩትን ስራ (እገታ እና ስለላ ማለት ይቀላል) አብረው የሚሰሩ? ነው ወይስ ያልገባኝ ነገር አለ? ይሄ ቢገባኝም እንኳን በ2 ወር ከአስር ቀኔ እንደምንም ያጠራቀምኩትን አዲስ ትውስታ ሁላ ነው የሚያጠፋብኝ።


መኪናው ቆመ። ከአይኔ ላይ ጨርቁ ሲነሳ መኪናዋ የቆመችው ከከተማ የራቀ ጭር ያለ ቦታ መሆኑን አስተዋልኩ። በቅርብ ርቀት የእኔ መኪና ቆማለች። እዚህ ደቂቃ ላይ ማመንም መጠራጠርም አይደለም የተሰማኝ። ምንም ነው!! ጎንጥ ግን የሆነ ነገር እንዳላማረው ያስታውቃል። ዙሪያ ገባውን ከቃኘ በኋላ እስከአሁንም ያልለቀቀውን እጄን አፈፍ አድርጎ ወደመኪናችን እየሄድን።

«ከአይናችን ተሰወሩ ማለት የሉም ማለት አደለም!! አሁን አንቺን ማጥፋት ቀላሉ መፍትሄያቸው ስለሆነ ማስታወስ ችለሽ ከምትፈጃቸው በፊት የአቅማቸውን ይሞክራሉ።» እያለኝ እኔን ባልያዘው እጁ ወገቡ ላይ ያለ ሽጉጡን ጨብጦ ወደኋላ እና ወደጎን እየተገለማመጠ መሬቱን በረጃጅም እርምጃው ይመትረው ጀመር። ያደረሰችን መኪና ከኛ በተቃራኒ አቅጣጫ ሄደች። ከአይናችን ስትሰወር መኪናችንጋ ደርሰናል። ስንቀርብ የመኪናችን ጎማ መተኛቱን አይቶ ጎንጥ ጎማውን በእግሩ ሲነርተው አየሁ።

ከየት መጣ ሳይባል አንድ ፒካፕ መኪና እየበረረ ፒስታውን መንገድ አቧራ እያጨሰ መጣ። እየሆነ ያለው ነገር ከመፈጣጠኑ የተነሳ ውዥብርብር አለብኝ። በቅፅበት የተኩስ ድምፅ ተሰማ!! ማናቸው ቀድመው እንደተኮሱ እንኳን አላውቅም ምክንያቱም ጎንጥም እየተኮሰ ነው። በየትኛው ቅፅበት ሽጉጡን እንዳወጣ እንኳን አላየሁም!! የትኛው ቅፅበት ላይ እጄን እንደለቀቀኝም አላውቅም! ማየት እስኪያቅተን የበዛ አቧራ እያቦነነ እና እየተኮሰ አልፎን የሄደው መኪና በሄደበት ፍጥነት አዙሮ ተመልሶ ወደእኛ ሲመጣ በአንድ እጁ የመኪናውን በር ከፍቶ

«ግቢ!! ገብተሽ ወደታች ዝቅ በይ!!!! ከወለሉ ተኝ!» ብሎ ጮኸ! ምንድነው እግሬን ከመሬቱ የሰፋው? እኔ የድርጊቱ አካል ያልሆንኩ ይመስል ዓይኔ አንዴ ጎንጥን አንዴ በፍጥነት እየመጣ ያለውን መኪና ያያል። በሩን ከፍቶበት በነበረው እጁ ከጎኑ ወደጀርባው ገፈተረኝ። አፈሰኝ ማለት ይገልፀዋል። እኔንም ራሱን መከላከል የማይችልበት አጣብቂኝ ውስጥ እንደከተትኩት ገብቶኛል ግን በምን በኩል ሰውነቴን ልዘዘው? ዓይኔ ስር ፊልም እየተሰራ ያለ ዓይነት ስሜት ነው ያለው። እኔን ወደጀርባው በደበቀኝ ቅፅበት ለጊዜው ምኑጋ እንደሆነ ያልለየሁት ቦታ እሱ ተመታ። እኔ የተመታሁ ዓይነት መሰለኝ። ጭንቅላቴ ለቅፅበት ያን ቦታ ትቶ ሄደ። ቅፅበት ናት ግን ድንዝዝዝ ያለ..... ብዥዥዥ ያለ ቅፅበት .... ጎንጥ የተመታበትን ቦታ በአንድ እጁ ይዞ

«ወዳጄ ይደርሳል። ከእርሱ ጋር ሂጂ!! እቤት እንዳትሄጅ!! » ይለኛል ጮክ ብሎ!!

«ትቼህማ አልሄድም!!» ዓይኔ ከፒካፑ መኪና ጀርባ እየመጣ ያለ መኪና በአቧራው ውስጥ ቢያይም ጭንቅላቴ ግን እዛው ገትሮኝ ሄዷል። አንድ ጥይት በጎኔ አልፎ መኪናውን ደነቆለው:: ሰውነቴ አይታዘዝም!! ደንዝዟል::

"ዝቅ በይ!" እያለ ይጮሃል ጎንጥ በከፊል ዘወር ሲል ከጎኑ የሚፈስ ደሙን እያየሁ ሀሳቤ ሄደ .... እዛ ቀን ላይ!!

ጥይቱ የተከፈተ የመኪናዬን መስኮት አልፎ ጡቴ ስር ሲመታኝ!! የመጀመሪያውን ህመም በቅጡ አስተናግጄ ሳልጨርስ ሁለተኛው ተመሳሳይ ቦታ ሲያገኘኝ። - የተመታሁ ቀን!! አንድ በአንድ ቁልጭ ብሎ ስዕሉ ጭንቅላቴ ውስጥ መጣ!! የማደርገው እና የማስበው በአንድ እኩል ቅፅበት ነበር። እጄን ማዘዜን አላስታውስም ብቻ ከጎንጥ እጅ ላይ ሽጉጡን እንደቀማው አውቃለሁ። ክፍቱን በተተወው የመኪና በር ግማሽ ሰውነቴን ከልዬ ሳደርገው የኖርኩት ልምዴ መሆኑን እርግጠኛ የሆንኩበትን ድርጊት እከውናለሁ። ከኋላ የመጣው መኪና በእኛና በፒካፑ መሃል ገብቶ ቆመ።

« ሂጅ እኮ አልኩ!!» ብሎ አምባረቀብኝ። በእጁ ጎኑን ደግፎ መሬቱ ላይ ተቀምጦ የመኪናውን ጎማ እንደተደገፈ።

«ደፋር እየሸሸ አይሞትም! እየተዋጋ እንጂ!» ስለው በህመሙ መሃል በስቃይ የታጀበ ፈገግታ አሳየኝ። ትውስታዬ ሳይከዳኝ በፊት አዘውትሬ የምለው አባባል ስለነበር ገባው። ጭንቀቱ የቀለለው መሰለ እና ህመሙን ማድመጥ ጀመረ። ፒካፕዋ መኪና ከአይኔ ራቀች። ወዳጄ ነው ያለው ሰውም ከመኪናው ወርዶ ወደኛ መጣ!! ሁለት ቦታ ነው የተመታው። አንዱ ከትከሻው ዝቅ ብሎ ሌላኛው ጎኑ ላይ የጎድን አጥንቶቹ መሃል ……. የለበስኩትን ሹራብ አውልቄ የሚንዥቀዥቅ ደሙን ለማቆም ከአንዱ ቁስል ወደ አንዱ እላለሁ።

« ሁሉንም?» ይለኛል አይኑን ላለመክደን እየታገለ።
« ምኑን ነው ሁሉንም?»
«ያስታወሽው?»
«መሰለኝ!!» አልኩት። ሁሉንም ላስታውስ የጎደለ ይኑረው በምን አውቃለሁ?

.......... ይቀጥላል........

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
543 viewsAbela, 16:55
Open / Comment
2023-04-13 19:55:09 የመኖር አካፋይ የመሞት ሲሶ መንገድ መሃል........


(ሜሪ ፈለቀ)

ክፍል 18

መቼም ሰው <ልቤ ዝቅ አለብኝ> የሚለው አሁን እኔ እንደሚሰማኝ ልቤ አቃፊዋን ለቃ የወጣች የሚመስል ስሜት ሲሰማ ነው የሚሆነው። የኔዋማ ዝቅ ከማለትዋም እነ ሳንባ ጉበትን <ዞር በሉ በናታችሁ> ብላ ገፋ ገፋ አድርጋ አንጀቴ ላይ ዛል ብላ ጋደም ያለች ይመስለኛል። አጅሬው እኔን ድዳና ሽባ አድርጎ በድንጋጤ አደንዝዞኝ እሱ እቴ በሙሉ አይኑ እንኳን አላየኝምኮ!!

ለመሆኑ ስሙስ የምር ጎንጥ ነው? የሚያወራው የሀገርኛ ለዛውስ ዘበኛ ለመምሰል ያስመሰለው ይሆን? ቅድም እንዴት ነበር ያወራው? ንፋስ ሲሆን ትከሻው ላይ ጣል የሚያደርጋት ፎጣውስ የትወናው አካል ትሆን? ዘበኛም ሆኖ አንዳንዴ ስንወጣ የሚለብሰውን ዓይነት ጅንስ በሸሚዝ ስለለበሰ የአለባበሱን ትወና መለየት ይቸግራል።

«ስራህንማ በአግባቡ ተወጣህ!» አለችው ሴትየዋ። ሙገሳ አይደለም! የሆነ ለበጣ ያለበት ነገር ነው! ቀጥላ የሆነ በእኔ ፊት ወይም በሰውየው ፊት መናገር ያልፈለገችውን ነገር ለብቻቸው እንዲያወሩ መሰለኝ። « ….. እኔ እና አንተ ብዙ የምናወራርደው ነገር አለ።» ብላ እጁን መንጨቅ አድርጋ ይዛው ልትሄድ ስትሞክር ከተቀመጠበት ሳይነሳ እጁን መነጨቃት። አስከትሎ ከእግሯ እስከ አናቷ በግልምጫ ካበጠራት በኋላ ራሱ ከተቀመጠበት ተነስቶ ቀድማው ከሳሎኑ እንድትወጣ ምልክት አሳያት። (እንደለመደው ነዳት ብል ይቀላል) በተጫማችው ሂል ጫማ እንደዝግዛግ ያለ አረማመድ እየረገጠች ሳሎኑን ለቃ ስትወጣ ተከትሏት እየተቆለለ ወጣ!! ከትውውቅ አልፈው መደነቋቋል ላይ የደረሱ ወዳጃማሞች መሆናቸውን ለማወቅ ምንም ሂሳብ አያስፈልግም!!

< ሄሎ!! እዚህ ነኝ! ሜላት! አስታወስከኝ? ከአንድ ቀን በፊት እመኚኝ ብለህ እንደወፍጮ ቤት እህል አየር ላይ ያንቀረቀብከኝ? አልታይህም?> ይላል ውስጤኮ አፌን ቃል ማን ያበድረው? ከሳሎኑ ከወጡ በኋላ የሚያወሩት ባይሰማኝም ጭቅጭቅ ላይ መሆናቸው ከድምፃቸው ያስታውቃል። ጎንጥ እንዲህ ይጮሃል እንዴ ሲያወራ? እኔ ንግግሩን ሳልሰማ ድምፁ እንዲህ ያስደነገጠኝ እሷ እዛች ሚጢጥዬ ፊቷ ላይ ሲጮህባት ወትሮም ያነሰች ፊቷ አለመትነኗ!!

የሁለቱ ሁኔታ ግራ የገባው ከመሰለው ሰውዬ ጋር ተፋጠን ሁለታችንም ከማይሰማው የሁለቱ ጭቅጭቅ ቃላት ለመልቀም ጆሯችንን አሹለን እንቃርማለን!! ፀጥ ያሉ መሰለ ወይም ድምፃቸው ለኛ መሰማቱን አቆመ።

«ለመሆኑ እኔ ማን እንደሆንኩ ታውቂያለሽ?» አለኝ ሰውየው በተፈጠረው ክፍተት። የሆነ ተራ ጥያቄ የጠየቀኝ አስመስዬ አፍንጫዬን ነፍቼ ለማለፍ ሞከርኩ።

«ጊዜ ግን ሲገርም!! በተሰቀለው!! ምንም ምንም አታስታውሺም?» ብሎ ሊገለፍጥ ዳዳው « መቼም ግፍሽ ነው!! በቁጥር እኮ አይደለም አንቺ የህዝብ ግፍ ነው ያለብሽ!! ሃሃሃሃ ሰውኮ የዘራውን ነው የሚያጭደው ሃሃሃ ስንቱን እንዳልከዳሽ የራስሽ ጭንቅላት ይክዳሽ? እረስታለች ሲሉኝ ማመን ያቃተኝ ቀጥ ብለሽ ስትመጪ ነው። ምንም የምታውቂው እና የምታስታውሺው ሳይኖር …… » ብሎ ሲጨርስ

«እኔ እንዳልረሳው አይጠፋህምሳ መቼም!» እያለ ገባ ጎንጥ!! ሴትየዋ ትንሽ ቀይ ፊቷ ሚጥሚጣ የተነፋበት ሰሃን መስሎ ተበሳጭታ ተከትላው ገባች።

«እሷ ትሄዳለች። ወንድምየው እኛጋ ይቆያል።» አለች በኮሳሳ ድምፅ ትዕዛዝም ሀሳብ ማቅረብም በመሰለ አነጋገር - ለሰውየው። ሰውየው ከተቀመጠበት ተነስቶ ሲደነፋ እና ሲጯጯሁ «ኪዳንን ትቼ አልሄድም!» ያልኩትን የሰማኝ የለም!! ጎንጥ አጠገቤ ደርሶ ቁጢጥ እንደማለት አለ እና

«እባክሽ እንዳታስቸግሪኝ (ይሄኛው ልመና ነገር ነበር) የምልሽን አድርጊ! ካለበለዚያ ያንቺንም የእኔንም የኪዳንንም ህይወት ነው እሳት ምትሰጅበት (ትዕዛዝ ነገር ሆነ) ለዛሬ! ለዝህች ደቂቃ ልታምኝኝ ይቻልሻል? (ልምምጥ ነገር ሆነ)» አልመለስኩለትም!! ሰውየውና ሴትየዋ በጥፍራቸው ቆመው ይጨቃጨቃሉ።

«ታምኚኛለሽ?» ሲል ግን በፍጥነት
«አላምንህም!!» አልኩት። ይህችን ለመተንፈስ ሰዓት እየጠበቅሁ ይመስል ተቅለብልቤ

«ሜላት እኔና አንቺ የምንነታረክበት ጊዜ የለንም! ስትፈልጊ አትመኚኝ ያልኩሽን ካልሰማሽ ሙት ነሽ!! (ይሄ ድብን ያለ ቁጣ ነው!!) እኔ እና አንቺ አሁን ወጥተን እንሄዳለን!! አንቺን እንጂ ኪዳንን አይፈልጉትም!! በምትወጅው ኪዳን ይሁንብሽ ለአንዴ እመኝኝማ! (እዚህጋ እኔን ማስረዳት የደከመው መሰለ) ኪዳን ምንም አይሆንም!! (ድምፁን ቀነስ አድርጎ) ኪስሽው ውስጥ አሁን እንዳታስታውቂ ! ኪዳን መልዕክት አኑሮልሻል!! ከዚህ ከወጣን በኋላ ታይዋለሽ!! አሁን እንሂድ? (ይሄ እባክሽ እንቢ እንዳትዪኝ የሚል ማባበል ነው።)።» ምላሴን ምን ያዘብኝ? እሺም እንቢም ማለት ጠፋኝ!! ሰዎቹ ጭቅጭቃቸውን ማቆማቸውን ያወቅኩት

« I knew it!! ወደሃት ነዋ!» ብላ እግሬ ስር ቁጢጥ ያለውን ጎንጥ በትንግርት እያየችው የሆነ ግኝት የተገለጠላት ዓይነት አስመስላ ስትጮህ ነው። ጎንጥ አቀማመጡን ገና አሁን ያስተዋለው ይመስል ተመንጭቆ ተነስቶ ክምር ተራራ አክሎ ተገተረ። ሴትየዋ አላቆመችም። እንደንቀትም፣ እንደ መገረምም ፣ እንደመናደድም …… እንደብዙ ነገር በሆነ ድምፅ እና እይታ « ጎንጥ ለዝህች? (በአይኗ አቅልላ የጤፍ ፍሬ አሳከለችኝ) ማን ያምናል? በምን አገኘችህ በናትህ?»

«አፍሽ ሲያልፍኮ አይታወቅሽም!! እረፊ ብያለሁ!» ብሎ ተቆጣ።

ቆይ እዚህጋ የትኛውን ሀሳብ አስቀድሜ የትኛውን አስከትዬ የቱን ምኑጋ ሰካክቼ ልከኛውን ምስል ላግኝ? ሰው ሀሳብ ይበዛበታል አይሉም በአንዴ ራሱን ጎንጥን የሚያካክል መአት ሀሳብ ወርውረውብኝ እዛ እንደተቀመጥኩ የሚዘነጉት? ኸረ ቆይ ጎንጥ ወዶኝ ነው የሚለውን ላስቀድም? ኸረ አይደለም! <ይህችን?> ብላ ምላሷ ላይ ያሟሸሸችኝ እኔ አስቀያሚ ነኝ እንዴ? አይደለም ኸረ ቆይ ጎንጥ ሴትየዋን ምን ቢላት ነው እኔን ይዞ እንዲሄድ የተስማማች? ኸረ ሌላው ደሞ እሱስ <ወድጃት አይደለም> ከማለት ይልቅ የሚደነፋው ወዶኝ ነበር ማለት ነው? አይ እነዚህ ሁሉ ይቅሩ እንዴት አምኜው ነው ኪዳንን ትቼው የምሄደው? ግን ምርጫስ አለኝ? ኸረ ኪዳን በምን ቅፅበት ነው መልዕክት ያስቀመጠልኝ? ምን ይሆን የሚለውስ? ደሞ ሌላ አለ እንጂ ቆይ ጎንጥ እኔን ቢወደኝ እሷ ምን እንዲህ ይንጣታል?

በአይኑ ከተቀመጥኩበት እንድነሳ ምልክት ሰጠኝ። በአይኑ አስነሳኝ። እጁን ሰጠኝ ወይም እጄን ተቀበለኝ እኔእንጃ ብቻ እጄን ያዘው እና ወደበሩ መራመድ ጀመረ። ጠባቂዎቹ ትዕዛዝ የሚጠብቁ ይመስላል ከበሩ አልተንቀሳቀሱም!! ሰውየው በአገጩ የሆነ ምልክት ሰጣቸው!! ከበሩ ገለል አሉ!! ሴትየዋ መናጥዋ በረታባት!!

«እመነኝ ጎኔ ይህችን አታልፋትም!! አስከፍልሃለሁ!! እመነኝ ትከፍላታለህ!!» አለች እየጮኸች። <ጎኔ> ብላ ነው ያቆላጰሰችው? ዛሬማ የሆነኛው ፊልም ተዋናይት ሆኛለሁ እንጂ እየሆነ ያለው እውን በእኔ ህይወት እየሆነ ያለ አይደለም!! እንዲህ አፍና ጭራው ያልተለየ እውነተኛ ህይወት ሊኖር አይችልም።
602 viewsAbela, 16:55
Open / Comment
2023-04-13 14:10:38 አወይ የሷ ነገር አወይ የሷ ስቅለት፤

በደል ሳይገኝባት ምግባር ሳይጎልባት፤

ተገርፋ በጥፊ ተመታ ላታሳልፍበት፤

መስቀሏ ላይነሳ ደንድኖ ሲሳናት፤

ቀራንዮን ስትመኝ ልታርፍ በስቅላት፤

ከወዴት ትሄዳለች? ጵላጦስ ሄሮደስ ሳይሆንባት ተርት።


በር ያለበት ሁሉ ቤተ መንግስት ሆኖ፤

ሄሮደስ ጵላጦስ በየበሩ ሞልቶ፤

እዝኛዉን ስትጨር ወደዝያኛው ተብሎ፣

ማለቂያ ያለው ዕለተ አርብ ጠፍቶ፤

ወዴት ትመጣለች ? ፍርድ ቤቱ በዝቶ።



አይዞሽ ትደሪሽያለሽ ታርፍያለሽ ተሰቅለሽ፤

ዳግም ላትቀምሽ የችንካሩን ጣእም ትቀምሽያለሽ ወደሽ፤

ቀራኒዮን በእምባ ጎልጎታን በዋይታ ትደርሽያለሽ መተሽ፤

ምጥሽ የከበደሽ ኢትዮጵያ እናቴ ይዞ የሚመጣ ያን ትንሳኤሽ ፤

ስቅለትሽ ይቅረብሽ እላለሁኝ እኔ።
(ስብሐት ወገን ከወላይታ)

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.3K viewsAbela, 11:10
Open / Comment
2023-04-13 08:46:23 ፅድቅ ነው አውቃለው .....
የሷን እጅ መያዝ
ድምጿን እየሰሙ በፈገግታ መጓዝ
ደሞ'ም ኩነኔ ነው ከሷ ጋራ መራቅ
ውሎ ማደር ከንቱ ሳይሰሙ የሷን ሳቅ

ፅድቅ ነው አውቃለው ...
ሀቅ እና እውነታ እምነት የሷ ድንበር
መታበይ የማያውቅ በዚች ከንቱ ምድር
.......
ከሰማይ የሰፋ የመታመን ጥጋት
ከባህር የሚልቅ የመውደድን ጥልቀት
በእፍኝ ቦታ ላይ አዛምዶ የያዘ
ልብሽ ነው አውቃለው ለፅድቅ የተጓዘ

እኔ ግን ተኮነንኩ ከሃጣን ተመደብኩ
እቅፏን ሰብሬ
ወዲያ አሽቀንጥሬ
ንፁህ ፍቅሯን ገፋው በስሜት ሰክሬ
ተስፋዋን አጨለምኩ መንፈሷን ረበሽኩ
ደስታዋን አጥፍቼ ፈገግታዋን ገደልኩ
.......
ግን አንድ እውነት አለ እሱንም አውቃለው
ከሃጢአት ለመዳን ንሰሃ ምርኩዝ ነው
ፍቅር መድህን ሆኖ ከመጣ ለህማም
ይቅርታ ፈውስ ነው ዳግም ለመታከም
......ዳሩ ግን
ከባድ ስለሆነ የበደሌ ስፋት
ምስኪኗ ልብሽን በይቅርታ መግፍት
እ.ን.ዳ.ላ.ስ.ቀ.ፅ.ፋ.ት
ምህረት አልጠይቅም ከደጅሽ ላይ ቆሜ
እንዴት አንቺን ላርክስ እኔ ተረግሜ
እናልሽ አለሜ
እናልሽ ተስፋዬ
እናልሽ ህመሜ
.......
ይቅር ባለማለት ሃጣን እንዳትባይ ኩነኔ እንዳትሰሪ
ቢያንስ አንቺ ኑሪልኝ ከፃድቃናት መሀል ስሜን እንድትጠሪ
መገኘት አለብሽ ከገነት አጥቢያ ላይ እውነቴን ለመንገር
መጥፎም ሆነ ጥሩ ታሪክ ይኖረዋል ወንድ ልጅ ሲያፈቅር!!!

By JAHA

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.9K viewsAbela, 05:46
Open / Comment
2023-04-13 00:44:20 Are You Single ?
97 viewspetelare Stay true, 21:44
Open / Comment
2023-04-13 00:15:00
ፊልም በነፃ ለማግኘት ይፈልጋሉ ? እንግዲያውስ ከታች መርጠው ይቀላቀላሉ ?

ትርጉም ፊልሞች..ተከታታይ እና single English ፊልሞች...የአሜሪካ ፊልሞች ና ድራማዎች በፈለጉት ጥረት ማግኘት ይችላሉ። ➪ይፍጠኑ
 
አሁኑኑ JOIN በማድረግ ይቀላቀላሉ
https://t.me/+X_b-HWVeRa41OWU0
446 viewspetelare Stay true, 21:15
Open / Comment
2023-04-12 21:46:28 » ብላ አጠገቤ ደርሳ የለበስኩትን ሹራብ ግልብ ስታደርገው ግራ ገባኝ እና መነጨቅኳት። የቆሙትን ጠባቂዎች (መሰሉኝ) ፊታቸውን እንዲያዞሩ ምልክት ስትሰጣቸው ሶፋው ላይ ያለው ሰውዬ እራቁቴን የማየት መብት እንዳለው ሁሉ ዝም አለችው። ከንግግሯ ምናልባት የምናወራውን የምቀዳበት ነገር ሰውነቴ ላይ ደብቄ እንደሆነ እያጣራች መሆኑ ገባኝ። በፓንት እና በጡት ማስያዣ ስቀር አይኑን ከሰውነቴ ላይ ለመንቀል ምንም ሀሳብ የሌለውን ሰውዬ እያየሁ መዋረድ አንገበገበኝ። ሴትየዋ ጡቴ ስር ገብታ ስታንቀረቅበኝ ጡቶቼን የምትመዝናቸው እንጂ የሆነ መቅጃ ያለችውን ነገር እየፈለገች አይመስልም። ጥርሴን ነክሼ ዋጥኩት። ሆነ ብላ የምታደርግ ነው የሚመስለው። ጣቷ የእንትኔን ጫፍ እስኪነካው ድረስ እጇን ፓንቴ ውስጥ ስትሰድ እስኪያማት ድረስ የእጇን አልቦ ማሰሪያ ጨመደድኩት።

«ok ok » ብላ እጇን አወጣች። የያዝኳትን ስለቀው ቦታው ደም መስሏል። ፊቷ ላይ ያስታውቃል። ከመፈተሿ በላይ እኔን ማዋረዷ ተመችቷታል። እንድለብሰው ልብሴን ከመሬት አንስታ ወረወረችልኝ። ከሰውየው ጋር ተያይተው ያልገባኝን መልዕክት ተለዋወጡ። ይዤው የነበረውን ቦርሳ አንስታ አመሳቅላ በረበረችው።

«አላመንከኝም እንጄ ነግሬህ ነበር,» አለችው። ሰውየው ባለችው ነገር ሙሉ በሙሉ ያመነ አይመስልም።

«እሺ ሜላት!! የታሉ ቪዲዮዎቼ?» አለ

«ወንድሜን በአይኔ ሳላየው ምንም ነገር አልነግርህም!!» አልኩት ለመኮሳተር እና ያልፈራ ለመምሰል እየሞከርኩ።

«ሜላት ይሄ ኔትፍሊክስ ላይ ተጥደሽ ስታዪ የምትውዪው የሆሊውድ ፊልም አይደለም። አጉል ጀግና ጀግና አትጫወቺ!! የትም አትደርሺም!!» አለ ልጥጥ ብሎ እንደተቀመጠ። አልመለስኩለትም።

«እየሰማሽኝ አይደለም? ዛሬ የምጫወትበትን ጠጠር የምመርጠው እኔ ነኝ። ያልኩሽን ነው የምታደርጊው።» ብሎ አምባረቀ።

«ወንድሜን ካላየሁ ምንም የማደርገው ነገር የለም አልኩ እኮ!!» ብዬ ለመጮህ ሞከርኩ።
ለቆመው አጭሩ ጠባቂ ምልክት ነገር ሰጠው። የታመቀ ትንፋሼን በረዥሙ ለቀቅኩት። ኪዳን ሲገባ ምንም የተጎዳ ነገር ያለው አይመስልም። ሲያየኝ ፊቱ ላይ ከቃላት በላይ የሆነ ስቃይ አየሁበት።

«I am so sorry» አለኝ ገና ስንተያየኝ። አልከለከሉኝም! ሄጄ አቀፍኩት። አጥብቆ አቀፈኝ። «ይቅርታ ሜል!»

«መልሰው!!» ብሎ ጮኸ ሰውየው። አብሬው እንድቆይ ብለምንም ሊሰማኝ እንኳን ግድ አላለውም። ምንድነበር ያሰብኩት? 'ናፍቆትሽ እስኪወጣልሽ እንጠብቅሻለን ከወንድምሽ ጋር ትንሽ ተወያዩ' እንዲሉኝ ነበር? የምርም እንዴት ያለ የቂል እቅድ ነው ያወጣሁት? ኪዳን ተመልሶ ሲሄድ የተሸነፍኩ መስዬ ላለመታየት ሞከርኩ። ሰውየው ወደእኔ አፈጠጠ።

«ሁሉንም ኮፒ እንዳመጣልህ አይደል ፍላጎትህ? በሰጠኸኝ አጭር ጊዜ ላመጣልህ አልችልም!! ተጨማሪ 24 ሰዓት ስጠኝ እና የምትፈልገውን በሙሉ እሰጥሃለሁ።» ስለው ያሳቃቸው ጉዳይ አልገባኝም ሁለቱም ከጣሪያ በላይ ሳቁ።

«ብዬህ ነበርኮ! በል ብሬን ወዲህ በል!» አለችው ሰትየዋ እጇን እየዘረጋች።

«እያወቅሽኝ ካላረጋገጥኩ መች አምናለሁ?» መለሰላት። እየሆነ ያለው ሙሉው ባይገባኝም እያላገጡብኝ እንደሆነ ገብቶኛል። ከኪሱ የሆኑ ብሮች ኖት አውጥቶ አቀበላት።

«ባንቺ ቤት አቃቂለሽኝ ሞተሻል!! ካንቺ ውጪ ማንም መረጃዎችሽን የት እንደምታስቀምጪ እንደማያውቅ ገምቻለሁ። እመቤትን ነበር የጠረጠርኩት እንደገባኝ እሷም የረዳችሽ ነገር የለም። አንቺም የት እንዳስቀመጥሽ እንዳታስታውሺ ትውስታሽ ላይመለስ ከድቶሻል። ንገሪኝ እስኪ ምን ልሁን ብዬ 24 ሰዓት ልጠብቅሽ?» ሲለኝ የበለጠ ጅልነት ተሰማኝ።

ባለፈው ከደበደቡኝ ጎረምሶች የተሻለ እነዚህ ሰዎች መረጃ ከፈለጉ በቀላሉ ማግኘት አይችሉም ብዬ እንዴት አሰብኩ? ምኗ ቂል ነበርኩ? አሁን ይገድሉኛል? እሺ ኪዳንንስ? ምንድነው ያደረግኩት?

በሩ ተከፍቶ የቅድሟ ሴት በሩ ላይ ላለው ጠባቂ የሆነ ነገር አንሾካሽኳ ወጣች። ጠባቂውም የሆነ ነገር ለሰውየው አንሾካሾከ። ሰውየው በጣም የተገረመ መሰለ።

«ያንቺው ጉድ ነው!» አላት ወደሴትየዋ እያየ። ሴትየዋ ግራ የተጋባች መሰለች። በጣም በመገረም ወደበሩ እያየች።
«ምን ልሁን ነው የሚለው አስገቡት እስኪ!»

ዓይኔ የሳተው ነገር ቢኖር ነው። ጆሮዬም እንደዛው? <የሷው ጉድ> ነው ያለው ወይስ <የአንቺው ጉድ> ነው ያለው? የእኔው ጉድ ጎንጥማ የሷው ጉድ ሊሆን አይችልም። ወይም ሌላ ጎንጥ ይሆናል እንጂ የእኔው ጎንጥማ አይሆንም!! በሩን አልፎ ሲገባ ቤቱ ነው የሚመስለው!! ልክ የእናት አባቱ ቤት እራት ሊበላ እንደመጣ ነገር ዘና ብሎ ከሶፋው ተሻግሮ ያለ ወንበር ሳብ አድርጎ ተቀመጠ።

እስከአሁን የነበረው ምኑም ያየኋቸውን ፊልሞች አይመስልም ነበር። ይሄ ግን ፊልም እንጂ እውን አይመስልም።

«ምን ትሰራለህ?» ብላ ሴትየዋ ጮኸች።

«ስራዬን ነዋ!!» አለ እንደማላገጥ ብሎ

ሆድቃዎቼ ቦታ የተቀያየሩ ነገር መሰለኝ። ሆዴ ውስጥ ተለዋወሰብኝ።

.......... ይቀጥላል........

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
1.5K viewsAbela, 18:46
Open / Comment