Get Mystery Box with random crypto!

Beza International Church

Logo of telegram channel bezachurch — Beza International Church B
Logo of telegram channel bezachurch — Beza International Church
Channel address: @bezachurch
Categories: Religion
Language: English
Subscribers: 2.09K
Description from channel

Beza International Church is a nondenominational Christian fellowship located in Addis Ababa, Ethiopia. The church was founded with the vision "Redeeming Nations in Righteousness!"
To connect with us, please reach out - @bezaconnect
Linktr.ee/bezachurch

Ratings & Reviews

1.67

3 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

2

1 stars

1


The latest Messages 7

2022-06-20 09:08:23
280 views06:08
Open / Comment
2022-06-20 09:07:55  የሰኞ ጠዋት ንባብዎ

ነፍሴን መለሳት
መዝሙረ ዳዊት 23: 3

የዚህን ሳምንት መልእክት ያመጣው ፓስተር ዘሩባቤል መንግስቱ ነው።

ይህ በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ ታዋቂ ምዕራፍ ነው፤ ምናልባት እኛም እነዚህን ጥቅሶች ብዙ ጊዜ ጠቅሰናቸው ይሆናል። ዛሬ እረኛው ነፍሳችንን እንደሚመልስ በሚናገረው ጥቅስ ላይ አተኩረን እንማራለን። የአማርኛውና ዋናው የአርማይክ ትርጉም የተጠቀሙት “ወደ ነበረበት ሁኔታ መመለስ” የሚለውን ፍቺ ሳይሆን “የወሰደውን መመለስ” የሚለውን ፍቺ ነው። ነፍስ እንዴት ትመለሳለች? ብለን ልንጠይቅ እንችላለን። ወዴትስ ልትሄድ ትችላለች? ብለንም ልንጠይቅ እንችላለን።

በአካል አንድ ቦታ ሆነን ነፍሳችን ስለሌሎች ነገሮች እያሰበች ሌላ ቦታ ልትሄድ እንደምትችል ሁላችንም እናውቃለን። ታላቁ እረኛ ኢየሱስ ነፍሳችንን ከሄደችበት በመመለስ ሟች ስጋ ለባሽ ሊያደርገው በማይችለው ሁኔታ ወደ ቀድሞው ሁኔታችን ሲመልሰን እናያለን።

ዛፉ
ኤርምያስ 17: 7- 8 “ነገር ግን በእግዚአብሔር የሚታመን መታመኛውም እግዚአብሔር የሆነ ሰው ቡሩክ ነው፤ በውሀ ዳር እንደ ተተከለ ሥሩንም ወደ ወንዝ እንደ ሰደደ ዛፍ ነው፤ ሙቀት ሲመጣ አይፈራም ቅጠሉም ዘወትር እንደለመለመ ነው በድርቅ ዘመን አይሠጋም ፍሬ ማፍራቱንም አያቋርጥም።”
 
መዝሙር 1: 1- 3 “በክፉዎች ምክር የማይሄድ፣ በኀጢአተኞች መንገድ የማይቆም፣ በፌዘኞችም ወንበር የማይቀመጥ ሰው ብፁዕ ነው። ነገር ግን ደስ የሚሰኘው በእግዚአብሔር ሕግ ነው፤ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያሰላስለዋል፤ እርሱም በወራጅ ውሀ ዳር እንደ ተተከለች፣ ፍሬዋን በየወቅቱ እንደምትሰጥ፣ቅጠሏም እንደማይጠወልግ ዛፍ ነው፤ የሚሠራውም ሁሉ ይከናወንለታል።” ሁለቱም ከላይ የተገለፁት ምንባቦች ስለዚህ  በውሀ ዳር ስለተተከለው ዛፍና እሱም እንዴት ፍሬያማ እንደሆነ ይናገራሉ። እያንዳንዳቸው ጥቅሶች የዚህ ዛፍ ባህሪ መገለጫ ስለሆነው መፅናት አንድ ጠቃሚና ቁልፍ የሆነ  ነገር ይሰጡናል።

ኤርምያስ ለፅናታችን ለመረጋጋታችን ምክንያቱ በጌታ ላይ ያለን መታመን መሆኑን ሲጠቅስ መዝሙር 1 ደግሞ የምንፀናውና  የምንረጋጋው ቃሉን ስናሰላስል መሆኑን ይናገራል። በመካከላቸው የሆነ ግንኙነት አለ፤ የመተማመን ችግር  እያጋጠመን ከሆነ ማሰላሰላችን የት እንዳለ መመርመር አለብን። የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰላችን በልባችን የነበረውን እምነት እንደገና ይመልሳል። እረኛው ነፍሳችንን የሚመልሳት በቃሉ ነው።

ምረቃ
በሉቃስ 4፡ 1- 11 ላይ ዲያብሎስ ኢየሱስን ሲፈትነው እናያለን። ኢየሱስም “ተፅፎአል” እያለ  በእግዚአብሔር ቃል ምላሽ መስጠቱን ቀጥሏል። በሦስተኛው ፈተና ሰይጣንም ቃል መጥቀስ ጀመረ። የሰይጣን ስትራቴጂ በእግዚአብሔር ቃልና በእምነት መካከል ክፍተትና ልዩነት መፍጠር ነው። ኢየሱስም በሌላ “ተፅፏል” ምላሽ ሰጥቶታል። እንደተተከለ ዛፍ የሚያደርገን ቃሉን ማወቃችን ሳይሆን በቃሉ ላይ ያለን እምነት ነው። በሁለቱ መሀከል ልዩነት አለ። ዛሬ የእግዚአብሔርን ቃል ከማወቅ የእግዚአብሔርን ቃል ወደ ማመን እንሻገር፤ በዚህም እንመረቅ።

የእምነታችን ሌላኛው ጎን
ሀና መፀነስ ስለማትችል በእጅጉ ተቸግራለች።1ሳሙ1 ነገር ግን ከጌታ ጋር ከተገናኘች በኋላ ፊቷ ላይ ዳግመኛ ሐዘን አለመታየቱን በ ቁጥር 18 ላይ ይናገራል። ከዚህ የነፍሷ መመለስ በኋላ ጌታ አሰባት። በዚህ የሚደንቀው መፀነሷ ብቻ አይደለም፤ ነገር ግን የአገሪቱን መድረሻ የቀየረ ነብይ ወለደች። በእግዚአብሔር ላይ ባለው የእምነታችሁ ሌላኛው ጎን ምን እየጠበቃችሁ ነው? በተመለሰች ነፍሳችሁ እግዚአብሔር ምን ማድረግ ይፈልጋል?

ማንኛውም የፀሎት ጥያቄ ካላችሁ በ @bezaconnect ይፃፉልን።
314 views06:07
Open / Comment
2022-06-20 09:07:28
330 views06:07
Open / Comment
2022-06-20 06:01:14 Here’s the Monday Morning Newsletter for our Sunday service by Pastor Zerubabbel:

"Meditating on the word of God restores trust in our hearts.!"
"የእግዚአብሔርን ቃል ማሰላሰላችን በልባችን የነበረውን እምነት እንደገና ይመልሳል!"

Your Monday Morning (June 20, 2022)
የሰኞ ጠዋት ንባብዎ (ሰኔ 13/ 2014)

https://bit.ly/BezaMMV17124

***
For prayer or to connect with Beza, reach out
ለፀሎት ወይም ከቤዛ ጋር ለመገናኘት በዚህ ያግኙን

@bezaconnect
357 views03:01
Open / Comment
2022-06-18 07:00:47
ሰላም የቤዛ ቤተሰብ!

የቅዳሜ ማለዳ ፀሎታችንን ጀምረናል፡፡

ከታች ያለውን አገናኝ በመጠቀም ይቀላቀሉ።


https://us02web.zoom.us/j/84216976202

ተባረኩ!
184 views04:00
Open / Comment
2022-06-17 16:01:57
ሰላም የቤዛ ቤተሰብ!

እንደተለመደው የቅዳሜ ማለዳ ፀሎታችን እንደተጠበቀ ነው።

ጠዋት ከታች ያለውን አገናኝ ይጠቀሙ።


https://us02web.zoom.us/j/84216976202

ቅዳሜ ከጠዋቱ 1-2 ሰዓት ድረስ እንገናኝ።፡


የጌታ ስም ይባረክ!

(ፕሮግራሙ በአማርኛ ቋንቋ ብቻ እንደሆነ እናስታውቃለን [For Amharic Speakers only])
170 views13:01
Open / Comment
2022-06-17 10:00:40
Hello everyone, we have Prayer Unusual today at 4:00 - 7:00PM (English Program) at Tabernacle in a hall in the basement of the new building.

Let's pursue God and seek His face together!!
215 views07:00
Open / Comment
2022-06-17 07:38:21  SAMARIA

A Devotional for June 17, 2022

"He had to pass through Samaria."
John 4: 4

The Jews never associated with the Samaritans, yet as we read in John 4: 9 "One day the Lord had to go through Samaria to teach His disciples."

While the disciples were going to buy some food, the Lord was tired and was sitting by the well of Jacob, a Samaritan woman came to draw water at noon. The Lord said to her, "give me a drink". In response, she asked him a question, "How can you, being a Jew, ask me the Samaritan woman for water? There are also rules that prevent you from doing this". Jesus replied, "If you knew who I was and that I had come to destroy all these walls you would have asked me and I would have given you the water of life so that you would not be thirsty again."

When she asked Him about superiority, Jesus said, "if you wish to speak on superiority, he who drinks from this superior well of yours will be thirsty again; but he that drinks the water that I give him shall never thirst." As He was speaking to her, his disciples saw Him and were surprised that He was talking to a Samaritan woman. But the Lord did not care about culture, tradition, religion, and gender, but about a person's life. As He said clearly, to save that soul, He had to go through Samaria."

What is our Samaria? It is something we never want to go through. But the Lord is showing us here that sometimes, we will have to go outside of the territory that we live in, the territory that we have warmed up to, our comfort zone. The Lord is saying, "Go to that forbidden village, because there are many people waiting for your testimony to be able to find salvation." Therefore, let us go with the Lord, who will satisfy the thirst for eternal glory beyond the boundaries which we have made; He wants us to break free. And we are called to be witnesses, not only in Judea, but also in Samaria.

Life Application
Let us go beyond the culture, tradition, law, and order and testify of the Lord that He is "worthy" just as in His Word. 

Prayer
Lord, help us to use the grace given to us because we have the truth and the grace that we need to leave our comfort zone and preach that there is no one more comforting and satisfying than you. Amen!

If you have any prayer requests, please write to us on @bezaconnect.
240 views04:38
Open / Comment
2022-06-17 07:38:04
171 views04:38
Open / Comment
2022-06-17 07:37:38 ሰማርያ

የሰኔ  10/ 2014 ቃል

“በሰማርያም ሊያልፍ ግድ ሆነበት።”
ዮሐንስ 4፥ 4

በዮሐንስ 4፡ 9 ላይ እንደምናነበው አይሁድ ከሳምራዊያን ጋር በፍፁም አይተባበሩም ነበር። ታዲያ ጌታ አንድ ቀን ለደቀመዛሙርቱ ሊያስተምር ፈልጎ "በሰማሪያ ማለፍ ግድ ሆነበት።"

ደቀመዛሙርቱ ምግብ ሊገዙ ሲሄዱ ጌታ ደክሞት በያዕቆብ ጉድጓድ አጠገብ ተቀምጦ ሳለ አንዲት ሳምራዊት ሴት በቀትር ውሀ ልትቀዳ መጣች፤ ጌታም ውሀ አጠጭኝ ሲላት ተገርማ ጥያቄ ጠየቀችው። አንተ አይሁዳዊ ሆነህ እንዴት ከእኔ ከሳምራዊቷ ውሀ ትጠይቃለህ? እኔ ሳምራዊት ሴት ነኝ፤ እንዲሁም ይህንን እንዳታደርግ የሚያግድህ ህግ አለ፤አለችው። ኢየሱስም በመገረም ማን እንደሆንኩ ብታውቂ ደግሞም ይህንን ሁሉ ግርግዳ ላፈርስ እንደመጣሁ ብታውቂ እኔን ትለምኝኝ ነበር፤ ዳግም እንዳትጠሚ የህይወትን ውሀም እሰጥሽ ነበር አላት። 

ዳግም ስለብልጫ ስትጠይቀው፤ ብልጫማ ካልሽ ከዚህ የሚጠጣ እንደገና ይጠማል፤ እኔ ከምሰጠው የሚጠጣ ግን ለዘላለም አይጠማም አላት። ከእሷ ጋር ሲነጋገር ደቀመዛሙርቱም አዩት፤ ከሴት ጋር ለዛውም ከሳምራዊት ሴት ጋር በመነጋገሩ ተገረሙ። ጌታ ግን ስለ ባህል፣ ወግ፣ ሀይማኖት እና ፆታ ሳይሆን ስለ አንድ ሰው ህይወት ግድ ይለዋል "በሰማርያ ሊያልፍ ግድ ሆነበት" እንደሚል ቃሉ።

ለኛ ሰማርያ የሆነብን በፍፁም በዛ ማለፍ የማንፈልግበት ጌታ ግን ሄዶ ያሳየን ክልል አበጅተን የተቀመጥንበት፣ እርስ በርሳችን የተሟሟቅንበት፣ ያ ክልክል ወደሚመስለን መንደር ጌታ ግን ሂዱ ያለን ለመዳን የኛን ምስክርነት የሚጠባበቁ ብዙዎች ስላሉ ነው። ስለዚህ ከሰራነው ክልል ውጭ በሰማርያ ወዳሉት ብልጫ ወዳለው ከዘላለም ጥማት የሚያሳርፈውን ጌታን ይዘን እንድንሄድ፤ ጥሰን እንድንወጣ ይፈልጋል። እናም በይሁዳ ብቻ ሳይሆን በሰማርያም ምስክሮቹ እንድንሆን ተጠርተናልና እንሂድ እንመስክር ቃሉን በእውነትና በፍቅር እንናገር።

የሕይወት ተዛምዶ
ከባህል፣ ከወግ፣ ከህግና ስርአት አልፈን ጌታ "ግድ ሆነበት" እንደሚል ቃሉ ከጌታ እርቀው ላሉት የሚበልጠውንና የሚያረካውን ጌታ እንድንመሠክር ግድ ይበለን ወደ እነሱ እንሂድ የያዝነውን እውነት በፍቅር እናሰረዳ።

ፀሎት
ጌታሆይ የያዝነው እውነትና የተቀበልነው ፀጋ ይዘን ከክልላችን እንድንወጣ እና ከምንም ነገር የምትበልጥ መሆንህን እንዳንተ የሚያሳርፍና የሚያረካ እንደሌለ እንድንናገር ነውና የተሰጠን ፀጋ እንድንጠቀምበት እርዳን። አሜን!

ማንኛውም የፀሎት ጥያቄ ካላችሁ በ @bezaconnect ይፃፉልን።
190 viewsedited  04:37
Open / Comment