🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ገራዶ ሚዲያ

Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Channel address: @geradomedia
Categories: News
Language: English
Subscribers: 679
Description from channel

🔸ሁሉን አቀፍ የመረጃ ምንጭ!🔸
✍ ፃፉልን @geradomediabot
fb.com/geradomedia
twitter.com/geradomedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 12

2021-04-22 14:53:47
#Ethio_Telecom #8100_A

ኢትዮ ቴሌኮም ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ተሳትፎ ማስተባበሪያ ብሔራዊ ምክር ቤት ጽህፈት ቤት ጋር በመተባበር በ8100 አጭር የፅሁፍ መልዕክት አማካኝነት ከደንበኞቹ የሰበሰበውን 122 ሚሊየን 467 ሺህ 676 ብር (ለግድቡ ግንባታ የሚውል) ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስረክቧል። #FBC

t.me/geradomedia
711 viewsGashu, 11:53
Open / Comment
2021-04-22 14:16:33
#ምርጫ_2013

የመራጮች ምዝገባ እንደሚራዘም ተጠቆመ!

በምርጫው ሂደት አስካሁን የነበሩትን ክንውኖች በሚመለከት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ከክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ጋር ውይይት አድርገዋል። ጠ/ሚኒስትሩ በውይይቱ ላይ “የኢትዮጵያ ጠላቶች ምርጫውን ለማስተጓጎል፣ ደካማና የሚያዙት መንግስት ለመፍጠር ሌት ተቀን እየሰሩ መሆኑን ልንገነዘብ ይገባል” ብለዋል። የዘንድሮው 6ኛው ብሔራዊ ምርጫ “ነጻ፣ ፍትሐዊ፣ ዴሞክራሲያዊ እና ሰላማዊ እንዲሆን በቁርጠኝነት እየሠራን ነው” ሲሉም ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች በምርጫው ሂደት የእስካሁኑን ክንውን ሪፖርት አቅርበዋል። በእስካሁኑ ሂደት የመራጮች ምዝገባ ተሳትፎ በጥሩ ሁኔታ የተከናወነባቸው ክልሎች መኖራቸው ተመልክቷል። በሲዳማና ኦሮሚያ ክልሎች እንዲሁም ድሬዳዋና አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደሮች የመራጮች ምዝገባ “ከ80 በመቶ በላይ” አፈፃፀም መኖሩን አብራርተዋል። በሌሎች ክልሎችም የመራጮች ምዝግባ አፈፃፀም ከ50 በመቶ በላይ መሆኑን ገልጸዋል።

በውይይቱ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመራጮች ምዝገባ እንደሚራዘም ጠቁመዋል። ተጨማሪው ቀን ምን ያክል እንደሚሆን ግን ቦርዱ ተወያይቶ የሚወስን እና የሚያሳውቅ መሆኑን ሰብሳቢዋ መገለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

t.me/geradomedia
481 viewsGashu, 11:16
Open / Comment
2021-04-22 14:15:22 ይህችን ምርጥ ቻናል ተቀላቀሏት! የፈለጋችሁትን ታገኙባታላችሁ!

ለመቀላቀል t.me/joinchat/RAn9b5UCOVFhyJKe
456 viewsGashu, edited  11:15
Open / Comment
2021-04-22 13:04:32
እናንተ ሶፋ ላይ ቁጭ ብላችሁ ማኪያቷችሁን እየጨለጣችሁ የድሃውን ልጅ እሳት ውስጥ አትክተቱት!
.
ፖለቲከኛ ነን ለምትሉ........

t.me/geradomedia
382 viewsGashu, 10:04
Open / Comment
2021-04-22 12:38:47
ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ ለሆኑ ጉዳዮች ጥቆማ መስጫ ስልክ ቁጥሮች፦

የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ህብረተሰቡ ማንኛውም ለፀጥታ ስጋት አጠራጣሪ የሆኑ ጉዳዮችን በሚመለከትበት ወቅት ከታች በተዘረዘሩት የስልክ ቁጥሮች አማካኝነት ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ አቅርቧል።

በአዲስ አበባ መረጃ መቀበያ ስልክ፦

- ልደታ ክፍለ ከተማ - 0118578492
- ቂርቆስ ክፍለ ከተማ- 0118578501
- አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ - 0118578499
- ቦሌ ክፍለ ከተማ - 0118578509
- የካ ክፍለ ከተማ - 0118578491
- ቃለቲ ክፍለ ከተማ - 0118578507
- ላፍቶ ክፍለ ከተማ - 0118578503
- ጉለሌ ክፍለ ከተማ - 0118578505
- አራዳ ክፍለ ከተማ - 0118578511
- ኮልፌ ክፍለ ከተማ - 0118578508

ሀገር አቀፍ የ24 ሰዓት መረጃ መቀበያ ስልክ፦

- 0115526302
- 816 , 987
- 0115526303
- 0115524077
- 0115543678
- 0115543681

#SHARE #ሼር

t.me/geradomedia
744 viewsGashu, 09:38
Open / Comment
2021-04-22 09:11:13
"ታጣቂዎች የሴዳል ወረዳን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ተቆጣጥረውታል" - ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በቤኒንሻንጉል ጉምዝ ክልል፣ ከማሺ ዞን የሚገኘውና ከ25 ሺህ በላይ ነዋሪዎች የሚገኙበት የሴዳል ወረዳ ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚችል ደረጃ ከሚያዝያ 11 ቀን 2013 ጀምሮ በታጣቂዎች ቁጥጥር ስር መዋሉን የደረሱት መረጃዎች እንዳመለከቱ አሳወቀ።

ኢሰመኮ ይህን ያሳወቀው ትላንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ነው።

ኮሚሽኑ በርካታ ነዋሪዎች፣ የወረዳው አስተዳደር እና ፖሊስ አካባቢውን ጥለው ወደ ተለያዩ ስፍራዎች መሸሻቸውን እንደተረዳ ገልጿል።

ታጣቂ ቡድኑ የመንግስትና የግለሰብ ንብረቶችን ማቃጠሉን፤ ነዋሪችን፣ የወረዳውን እና የዞን አመራሮችን እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞችን መግደሉን እና ማገቱም ተገልጿል።

ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በአቅራቢያው ያለው የፀጥታ ኃይል ከአቅሙ በላይ እንደሆነና ተጨማሪ የተላከው ኃይልም ወደ አካባቢው እንዳልደረሰ ገልፀዋል።

ይህ ክስተት በክልሉ የቆየው የጸጥታ ችግር እየተባባሰ እና መልኩን እየቀየረ መምጣቱን የሚያሳይ በመሆኑ ከፍተኛ ስጋት የሚያሳድር ነው ብሏል ኢሰመኮ።

ኮሚሽኑ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተለ መሆኑን በመግለፅ፥ ከሚመለከታቸው የፌዴራል እና የክልል መንግስት አካላት ጋር በመነጋገር ላይ መሆኑን አሳውቋል።

ኢሰመኮ መንግስት በአፋጣኝ የአካባቢውና የክልሉን የፀጥታ ኃይል እንዲያጠናክርና እና ተጨማሪ የሰዎች ሞትና የከፋ ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት እንዳይከሰት እንዲከላከል ጥሪ አቅርቧል።

t.me/geradomedia
397 viewsGashu, 06:11
Open / Comment
2021-04-22 09:10:58 ይህችን ምርጥ ቻናል ተቀላቀሏት! የፈለጋችሁትን ታገኙባታላችሁ!

ለመቀላቀል t.me/joinchat/RAn9b5UCOVFhyJKe
350 viewsGashu, edited  06:10
Open / Comment
2021-04-21 20:09:39
#FAKE_NEWS

"የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር የሆኑት አቶ መላኩ አለበል በገዛ ፍቃዳቸው ስራቸውን ለቀዋል" እየተባለ በማህበራዊ ሚዲያ የሚናፈሰው ወሬ የሀሰት መሆኑን የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ አስታውቋል። ሚኒስትሩ ስራ ላይ ናቸው።

t.me/geradomedia
218 viewsGashu, 17:09
Open / Comment
2021-04-21 20:09:28 ይህችን ምርጥ ቻናል ተቀላቀሏት! የፈለጋችሁትን ታገኙባታላችሁ!

ለመቀላቀል t.me/joinchat/RAn9b5UCOVFhyJKe
212 viewsGashu, edited  17:09
Open / Comment
2021-04-21 13:00:44
ጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለሱዳን ጠ/ሚ ዶ/ር አብደላ ሃምዶክ ጥሪ ምላሽ ሰጥተዋል!

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ለሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ በሚያዝያ ወር መጀመሪያ ላይ ለጻፉት ደብዳቤ ምላሽ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያም የወቅቱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀ መንበር እና ለዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ፕሬዚዳንት ፌሊክስ ሺሴኬዲ ከግድቡ ጋር በተያያዘ ባሉ መጓተቶች ላይ ስብሰባ እንዲጠሪ ሃሳብ አቅርባለች፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ እስካሁን በግድቡ ዙሪያ የተካሄደው ውይይት እንዳልተሳካ መቁጠር አግባብ አለመሆኑን ጠቅሰው፥ ለዚህም እንደ የመርሆዎች ስምምነት መፈረም እና የብሔራዊ ገለልተኛ የሳይንስ ምርምር ቡድን መመስረትን በመልካም ማሳያነት አንስተዋል፡፡

በግድቡ ዙሪያ የሚደረጉ ድርድሮች ህጋዊና ቴክኒካዊ ተግዳሮቶች ሁሉንም አሸናፊ የሚያደርጉ ስምምነቶች ላይ ለመድረስ እንቅፋት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የአፍሪካ ህብረት ለዘጠኝ ጊዜያት ያህል መስተጓጎል የገጠመውን የሦስትዮሽ ድርድር ዕውን እንዲሆን ያደረገው ጥረት አድነቆታቸውን ገልጸዋል፡፡

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ፥ ኢትዮጵያ በሕዳሴ ግድብ ላይ የሚካሄደው የሦስትዮሹ ድርድር አሁንም ቢሆን በአፍሪካ ህብረት ጥላ ስር ሆኖ እንዲቀጥል ጽኑ ፍላጎትት እንዳላት በደብዳቤያቸው ስለመግለፃቸው ኤፍ ቢ ሲ አስነብቧል።

t.me/geradomedia
805 viewsGashu, 10:00
Open / Comment