Get Mystery Box with random crypto!

ገራዶ ሚዲያ

Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Channel address: @geradomedia
Categories: News
Language: English
Subscribers: 679
Description from channel

🔸ሁሉን አቀፍ የመረጃ ምንጭ!🔸
✍ ፃፉልን @geradomediabot
fb.com/geradomedia
twitter.com/geradomedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 60

2021-02-01 18:06:30
ለ12ኛ ክፍል ፈተና የሚያስፈልጉት 400 ሺህ ታብሌቶች ወደ አገር ውስጥ አልገቡም ተባለ!

የትምህርት ሚኒስቴር የ12ተኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበትን 'ቁርጥ' ያለ ቀን እንዲያሳውቅ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት አሳስቧል። የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ሚሊዮን ማቲዮስ በበኩላቸው፥ "ፈተናው የሚሰጥበትን ቀን ለማሳወቅ ለፈተናው የሚያስፈልጉት 400 ሺህ ታብሌቶች ወደ አገር ውስጥ አልገቡም" ብለዋል።

ለዚህም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጋር እንደሚሰራና 'ታብሌቶቹ' ወደ አገር ሲገቡ ፈተናው የሚሰጥበት ቀን እንደሚወሰን ተናግረዋል። የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን ለማቀላጠፍ በ1 ሺህ 500 የፈተና ጣቢያዎች አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን እንዳስረዱ ኢዜአ ዘግቧል።

t.me/geradomedia
5.5K viewsGashu, 15:06
Open / Comment
2021-02-01 10:45:51
5.6K viewsGashu, 07:45
Open / Comment
2021-02-01 10:09:40
#በማይናማር_የወታደሩ_ስልጣን_መያዝ

በቀድሞ በርማ በአሁኗ ማያንማር ወታደሩ ሥልጣን መቆጣጠሩ ተሰምቷል። ወታደሮች ሥልጣን መቆጣጠራቸውን ይፋ ያደረጉት የሲቪል መንግሥት አባላትን በቁጥጥር ሥር ማድረጋቸውን ተከትሎ ነው።

የኖቤል ተሸላሚዋ ኦንግ ሳን ሱ ቺ እና ሌሎች የፖለቲካ መሪዎች ተለቅመው ወዳልታወቀ ሥፍራ ተወስደዋል። በማይናማር በወታደሩ እና በሲቪሊያን አስተዳደሩ መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ውጥረት ተከስቶ ነበር።

እነ ሳን ሱ ቺ ከመታሰራቸው ቀደም ብሎ የመንግሥት ቴሌቪዥን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አውጆ ነበር። ሚየንማር የዲሞክራሲያዊ ማሻሻያዎችን ማድረግ እስከጀመረችበት 2011 ድረስ በጥብቅ ወታደራዊ መንግሥት ነበር ስትመራ የቆየችው።

ባለፈው ሕዳር ወር በተደረገ ምርጫ የሳን ሱ ቺ ፓርቲ 'ናሽናል ሊግ ፎር ዲሞክራሲ' መንግሥት ለመመሥረት የሚያስችለውን የመቀመጫ ቁጥር ማግኘት ችሎ ነበር። ሆኖም ወታደሮቹ ምርጫው ተጭበርብሯል ሲሉ ቆይተዋል።

በዛሬው ዕለት የሀገሪቱ ወታደሮች የአገሪቱን ሥልጣን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውና መሪያቸውም ኮማንደር ሚነ ኦንግ ሌይንግ መሆናቸው ተናግረዋል። ወታደሩ ለአንድ ዓመት በስልጣን ላይ እንደሚቆይም ገልጿል።

በርካታ ወታደሮች በአገሪቱ ዋና ከተማ ናይፒታው እና በሌላኛዋ ዋነኛ ከተማ ያንጎን ይታያሉ። በርካታ ወታደሮች በተለያዩ ቦታዎች እየሄዱ የሲቪል አስተዳደሩ ሚኒስትሮች የነበሩ ሰዎችን በቁጥጥር ሥር እንዳዋሉ ቤተሰቦቻቸው ተናግረዋል።

የሞባይል እና ኢንተርኔት አገልግሎት እንዲሁም ስልክ በስፋት የተቋረጠባቸው ዋና ዋና ከተሞች ላይ ሲሆን የአገሪቱ ብሔራዊ ቴሌቪዥን ሥርጭት ለማድረስ እክል እንደገጠመው በመግለፅ ተቋርጧል።

Via BBC , Tikvah

t.me/geradomedia
4.8K viewsGashu, 07:09
Open / Comment
2021-01-31 22:33:52
የካይሮ ደላሎች ያሰናዱት አቤቱታ ለባይደን መንግስት

(በእስሌማን አባይ - የዓባይ ልጅ)

ግብፅ የቀጠረችው የጉዳይ እንደራሴ ተቋም ፀረ-ህዳሴ ግድብ አቤቱታ አደራጅቶ ለባይደን መንግስት ለማቅረብ ቀጠሮ ይዟል። የግብፅን ጉዳይ በእንደራሴነት የያዘው የሎቢ ኩባንያ ነው አዲሱን የአሜሪካ መንግስት ለማግባባት መርሃግብር ቀርፆ መድረክ ያዘጋጀው።

የህዳሴ ግድቡ አካባቢያዊ ተፅዕኖው እጅግ ከፍተኛ ነውና የባይደን መንግስት ይህን እንዲገነዘብ እንሰራለን እያለም ይገኛል፤ ኩባንያው። ለዚህም በዋሽንግተን የሚገኘው የግብፅ ኢምባሲ ነገ feb, 1 ባዘጋጀው የዙም ኮንፈረንስ ላይ ለማግባባት ተግባራቸው ይጠቅሙኛል ያላቸውን አካላት ተሳታፊ እንዲሆኑ የሎቢ ድርጅቱ ጥሪ አድርጓል። በኮንፈረንሱ የተሳታፊዎች መጥረያ ደብዳቤ ላይም የሎቢ ኩባንያው በነጩ ቤተ መንግስት አካባቢ ጥበቃ ላይ የሚያተኩረው "International Conservation Caucus" ይቋቋም ዘንድ ከዋነኛ መስራቾች ውስጥ እንደነበረ አስታውሷል።

ነገ ሊካሄድ ባቀዱት ኮንፈረንስ ላይ የግብፅ መስኖ ሃይድሮሊክ ፕሮፌሰር ሒሻም በኪህ፣ የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የህግ አማካሪ ሙሐመድ ሂላል ተሳታፊ ይሆናሉ። ትራምፕ ተሸንፈው ጅጆ ባይደን ወደ ዋይት ሐውስ መምጣታቸውን ተከትሎ በየወሩ 65 ሺ ዶላር እየተከፈለው ለማግባባት ተግባር የተፈራረመውን Brownstein Hyatt Farber Schreck በፖሊሲ ዳይሬክተርነት የሚመራው Royce እንዲሁ የኮንፈረንሱ ተሳታፊ ናቸው።

t.me/geradomedia
5.5K viewsGashu, edited  19:33
Open / Comment
2021-01-31 20:50:43 #በዋሽንግቶን_ዲሲ_የተካሄደው_ሰልፍ

ከሰሞኑ በሺዎች የመቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በትግራይ ክልል እየደረሰ ነው ያሉትን ሰብዓዊ መብት ጥፋት፣ እና የመብት ረገጣ በመቃወም በዋሽንግቶን ዲሲ ሰልፍ አድርገው ነበር።

ሰልፈኞቹ በትግራይ ህዝብ ላይ ዘር የማጥፋት ጦርነት ታውጇል ይህንን ነው የምንቃወመው ብለዋል፤ "ይህንን የምንለው እየተገደለ ያለው የፖለቲካ መሪ ብቻ ስላልሆነ፤ የሚገደሉት ንፁሃን ዜጎች ጭምር ስለሆኑ ነው" ሲሉ ይገልፃሉ።
አክለውም እየተሰደዱ እየተገደሉ፣ ንብረታቸው እየተቃጠለ እና እየተዘረፉ ያሉት ንፁሃን ናቸው ብለዋል።

በትግራይ ክልል ሴቶች እየተደፈሩ፣ እየተገደሉ ነው እነዚህ ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው ያሉት ንፁሃን የትግራይ ተወላጆች እንጂ የTPLF አመራሮች አይደሉም ሲሉ ተናግረዋል፥ በዚህ ምክንያት ነው ዘር የማጥፋት ተግባር ነው የምንለው ብለዋል። እነዚህ ሰልፈኞች በትግራይ ክልል እየደረሰ ያለው በደል እንዲቆም የአሜሪካ መንግሥት ጣልቃገብነት እንደሚያስፈልግ አስረድተዋል።

የአሜሪካ መንግስት (የትራምፕ አስተዳደር) ጦርነቱን በይፋ ወጥቶ አልተቃወመም፤ የባይደን አስተዳደር ላይ ያሉ ሰዎች ግን ጉዳዩ እንደሚሳስባቸው እየገለፁ ነው ነገር ግን ይህ በቂ አይደለም ብለዋል።

የአሜሪካ መንግስት የውጭ ኃሎች ከትግራይ በአስቸኳይ ሙሉ በሙሉ እንዲወጡ እንዲያደርግ፣ ለሰብዓዊ ድጋፍ መንገድ ክፍት እንዲደረግ ጫና እንዲያሳድር እንጠይቀለን ብለዋል።

ከሰልፍ አስተባባሪዎች መካከል መኣዛ ግደይ፥ "በትግራይ ክልል ሰዎች እየተራቡ ያሉት ምግብ ስለታጣ አይደለም፤ መንገድ ነው የጠፋው፣ የትግራይ ተወላጆች ብር አዋጥተናል እጃችን ላይ ይገኛል፥ አለም አቀፍ NGO እርዳታ ይዘው እየተጠባበቁ ነው፤ አብይ አህመድ እና ደጋፊዎቹ መንገዱን አንከፍትም ስላሉ ህዝቡ ረሃብ አጋጥሞታል" ብላለች።

በአሜሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር ፍፁም አረጋ ሰልፉ በህግ ማስከበር ዘመቻችን ድል የተደረጉ አካላት ደጋፊዎች እና ተባባሪዎች የጠሩት፤ ብዙዎችን አሳስተው የመሩት ነው" ሲሉ ድርጊቱን አውግዘዋል።

ኣምባሰደር ፍፁም፤ በመንግስት ላይ እየቀረበ ያለውን የዘር ማጥፋት ክስ ውድቅ አድርገዋል። መንግስት ክልሉን ለማረጋጋት "ፅንፈኛው የህወሓት ኃይል" ያፈራረሳቸውን መሰረተ ልማቶች የመጠገን እና የነፍስ አድን ቁሳቁሶች የማድረስ ተግባር የኢትዮጵያ መንግስት እየሰራ መሆኑን አሳውቀዋል።

አክለውም መንግድት አሁን ላይ 92 ምግብና መድሃኒት ማሰራጫ ጣቢያዎች ወደነበሩበት መልሷል፤ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በየአካባቢው አስተዳዳሪዎችን እያስመረጠ እሰራ ነው ያለው፤ ለክልሉ ተገቢው ድጋፍ እየተደረገ ነው ብለዋል።

አምባደር ፍፁም አረጋ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ከኤርትራ መንግስት ጋር በመተባበር በክልሉ ነዋሪዎች ላይ የመብት ረገጣ እየፈፀመ ነው ለሚለውም ክስ እንደማይቀበሉት ገልፀው የቀድሞ የህወሓት አስተዳደት ፈቶ በለቀቃቸው በሺዎች የሚቆጠሩ የቀድሞ እስረኞሽ የሚፈፀሙ ወንጀሎችን ለመቆጣጠር መንግስት እየሰራ ነው ብለዋል።

አምባሳደር ፍፁም፥ "...የኤርትራ መንግስት (በትግራይ ክልል ጉዳይ) ተሳትፎ እንዳልነበረው እራሳቸው መግለጫ ሰጥተዋል፤ በኢትዮጵያ መንግስት በኩል ለኤርትራ መንግስት የተደረገ ግብዣ እንደሌለ ከነሱ ጋር በመተባበር የተሰራ ስራ እንደሌለ በተደጋጋሚ ገልጿል። ሌላው የሚሰማው በርካታ ወንጀለኞችን ፈተው በመሄዳቸው ወደ 13 ሺህ የሚጠጉ እስረኞች ተፈተዋል ተብላል ከዚህ ጋር በተያያዘ የሚያጋጥሙ ወንጀሎችን ለመከላከል መንግስት ከህዝቡ ጋር በመሆን ከፍተኛ ስራ እየሰራ ነው" ብለዋል።

"ከአሁን በፊት ከፍተኛ የሆነ ጭፍጨፋ በማይካድራ ተፈፅሟል፤ በማይካድራ የተካሄደው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን፣ ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተቋማትም ትልቅ አፅንኦት ሰጥተው ቀጣይ ምርመራ እየተደረገበት ነው ያለው። ሌላ ከዛ የተለየ ነገር በሌሎች አካባቢዎች በግጭቱ ያጋጠሙ ጉዳቶች ካልሆነ በስተቀር የሰማነው የለም። ነገር ግን መንግስት ለማጣራት ክፍት ነው። በመንግስት በኩል ይሄን ሆን ብሎ የሚያደርግበት ምንም ምክንያት የለውም፤ ዜጎችን ለማዳን እየሰራ ነው። ሁሉም ወገኖቻችን ናቸው። ግን እኛ ባልነው መንገድ ካልሆነ በስተቀር ሀገሪቱ ትፍረስ የሚል አቋም የያዙ ኃይሎች በሚዲያው በሶሻል፣ በመደበኛ ሚዲያው፣ ከፍተኛ የሀሰት ፕሮፖጋንድ በስፋት እየረጩ ነው ያሉት፤ እውነት እንደሆነ ይዘገያል እንጂ እያደር መጥራቱ አይቀርም" ብለዋል አቶ ፍፁም።

Via VOA, Compiled by #Tikvah

t.me/geradomedia
5.5K viewsGashu, 17:50
Open / Comment
2021-01-31 20:50:20
5.0K viewsGashu, 17:50
Open / Comment