🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ገራዶ ሚዲያ

Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Channel address: @geradomedia
Categories: News
Language: English
Subscribers: 679
Description from channel

🔸ሁሉን አቀፍ የመረጃ ምንጭ!🔸
✍ ፃፉልን @geradomediabot
fb.com/geradomedia
twitter.com/geradomedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 51

2021-02-13 21:24:06 #የትግራይ_ክልል_ወቅታዊ_ሁኔታ

በመቐለ ከተማ 80% የመንግስት መስሪያ ቤቶች ወደ ስራ መመለሳቸው፦

በመቐለ ከ80 በመቶ በላይ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ወደመደበኛ ስራ መመለሳቸውን እና ህዝቡን ማገልገል እንደጀመሩ የመቐለ ከተማ የመንግስታዊ አገልግሎት ገልጿል።

የከተማው የመንግስት አገልግሎት ዘርፍ ምክትል ኃላፊ መምህር ገብረኪሮስ ህሉፍ፥ "በገጠመው የመፀጥታ ችግር ምክንያት በርካታ ቁሳቁሶች በመውደማቸው ምክንያት እስካሁን አገልግሎት መስጠት ያልጀመሩ የተወሰኑ መስሪያ ቤቶች እንዳሉ ገልፀው መስሪያ ቤቶቹ ወደስራ እንዲመለሱ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር እየተሰራ መሆኑን አሳውቀዋል።

በየመስሪያ ቤቱ ኮፒዩተር፣ የፅህፈት መሳሪያ የመሳሰሉት ወድመዋል፤ ተዘርፈዋል። የጠፉ ንብረቶች ተጠንተው ወደሚመለከተው አካል ሪፖርት መደረጉን እና ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ጋር በመሆን አስፈላጊውን ቁሳቁስ ለማሟላት እየተሰራ መሆኑን መምህር ገብረኪሮስ ህሉፍ ተናግረዋል።

የትግራይ መልሶ ማቋቋም ስምምነት ከUNDP ጋር

በትግራይ መልሶ ግንባት ላይ ድጋፍ ለማድረግ UNDP ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አሰተዳደር እና ከኢፌዴሪ ገንዘብ ሚኒስቴር ጋር ስምምነት ተፈራርመዋል።

የገንዘብ ሚኒስቴር በትግራይ ያሉ ተቋማት የመለሶ ግንባታ ስራ ተጠናቆ በቅርቡ ሁሉም ስራ እንደሚጀምር አሳውቋል።

በትግራይ ክልል ግብር የመሰብሰብ ጉዳይ

ከትግራይ መልሶ ማቋቋም ጎን ለጎን ግብር የመሰብሰብ ስራ እንደሚቀጥል የክልል ትግራይ ጊቢዎች ባለስልጣን አሳውቋል።

የክልል ትግራይ ገቢዎች ባለስልጣን በመቐለ ካለው የተሻለ ሰላም እና ፀጥታ አንፃር ሁሉንም ፅ/ቤቶቹን ከፍቶ መደበኛ ስራ መጀመሩን ገልጿል።

ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ምንም እንኳን በመቐለ እንደመነሻ መደበኛ ስራውን ቢጀምርም በዞን እና በወረዳ ካለው ጊዜያዊ አስተዳደር ጋር በሚደረግ ውይይት ከሌሎች መስሪያ ቤቶች ጎን ለጎን ፅ/ቤቶቹ እንዲከፈቱ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አሳውቋል።

ሰላም ሚኒስቴር የሚደረገው ድጋፍ መቀጠሉን ማሳወቁ

በትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ የምግብና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶች ስርጭት እስከ አሁን በ32 ዞኖችና ወረዳዎች በሚገኙ 92 የስርጭት ጣቢያዎች ተጠናክሮ መካሄዱን ቀጥሏል ሲል አሳውቋል።

በተመሳሳይ ድጋፉ በክልሉ በሚገኙ ሁለት የስደተኞች መጠለያ ካምፖች እየተዳረሰ እንደሚገኝ ገልጿል።

በትግራይ የቀጠለው አድማ እና ተቃውሞ የሰዎችን ህይወት መቅጠፉ

በትግራይ ክልል ግፍ እየተፈፀመ፣ የሃይማኖት መሪዎች እየተገደሉ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉዳት እየደረሰባቸው ባለበት ወቅት የኢትዮጵያ የሃይማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማግሌዎች ድርጊቱን ሳያወግዙ ወደ ትግራይ ክልል መምጣታቸው ትክክል አይደለም በሚል ምክንያት የተነሳው ተቃውሞ/አድማ በተለያዩ ከተሞች ቀጥሏል። 

ተቃውሞው ከመቐለ ጀምሮ ወደ ውቅሮ፣ ፈረወይኒ፣ እዳጋሃሙስ፣ ዓዲግራት፣ አድዋ፣ ሽረ ፣ አክሱም ከተሞች ነው የተስፋፋው።

በከተሞቹ የሃማኖት አባቶች እና የሀገር ሽማጌዎች መጥተዋል በሚል ነው ተቃውሞ የተነሳው። በመቐለ በተቃውሞ እና አድማ ተቋርጦ የነበረው እንቅስቃሴ ከትላንት ጀምሮ ወደመደበኛው ሁኔታ ተመልሷል።

የትራንስፖርት (ታክሲ አገልግሎት) ጀምሯል፣ ንግድ ተቋማት፣ አገልግሎት ሰጪዎች ተከፍተዋል መደበኛ የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ተመልሷል።

በአክሱም ከሀሙስ ጀምሮ ነው ተቃውሞ የተቀሰቀሰው፤ ተቃውሞው የኢትዮጵያ የሀገር ሽማግሌዎች እና የሃይማኖት መሪዎች ገብተዋል በሚል የተቀሰቀሰ ሲሆን መንገድ የመዝጋት፣ ጎማ የማቃጠለ ሁኔታዎች እንደነበሩ ተሰምቷል።

እያሱ ተስፋይ የተባሉ የከተማው ነዋሪ ትላንት ምሽት በነበረው የአሜሪካ ድምፅ የሬድዮ ጣቢያ መደበኛ ስርጭት አማርኛው ክፍል በሰጡት መረጃ በተነሳው ተቃውሞ የመከላከያ እና የኤርትራ ኃይል ተኩስ በመክፈቱ 7 ሰዎች መሞታቸውን እና 4 ሰዎች መቁሰላቸውን ገልፀዋል። በ3ቱ ሰዎች ቀብር ላይም እንደነበሩ አሳውቀዋል።

የኤርትራ ሰራዊት በከተማው ስለመኖሩ በምን እንደለዩ የተጠየቁት የከተማው ነዋሪ የሚጠቀሙበት መኪና የኤርትራ ታርጋ ያለው መሆኑን እና በሚለብሱት መለዮ እንደሚለዩ ገልፀዋል።

በውቅሮ ከተማ በነበረው ተቃውሞ 17 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉትን ኣንዲት የከተማው ነዋሪ ተናግራለች። 

ይህች መረጃውን የሰጠች የወቅሮ ከተማ ነዋሪ ሁለት ጎረቤቶቿ ከሟቾች መካከል እንደሚገኙ ገልፃለች።

በከተማዋ መንገዶች በተዘጉበት ወቅት መንገዶችን ክፍቱ በሚል ነበር ተኩሱ የተከፈተው ፤ የተኩሱንም ድምፅ ሰምተው ይሮጡ የነበሩ ሰዎችም በጥይት ተመተው መገደላቸውን ተናግራለች።

በሽረ እንደስላሴ ከተማ በተቃውሞ ምክንያት በተተኮሰ ጥይት 4 ሰዎች መሞታቸውን ወልደስላደ መኮንን የተባለ የከተማው ነዋሪ ተናግሯል።

በከተሞቹ የትራንስፖርት መቋረጥ፣ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መዘጋት አድማ እንደትላንት ድረስ ቀጥሎ መዋሉን ጋዜጠኛ ሙልጌታ አፅብሃ ዘግቧል።
የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ኮሚኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ ኢተነሽ ንጉሰ ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉ መሆኑና ስለተፈጠረው ሁኔታ ሙሉ መረጃ እና ማብራሪያ እንደሚሰጥ ገልፀዋል።

የዶክተር ሙሉ ነጋ ከኢዜአ ጋር የነበራቸው ቆይታ

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈፃሚ በክልሉ ባለፉት ሁለት እና ሶስት ቀናት ስለነበረው ሁኔታ ግልፅ ማብራሪያ ባይሰጡም የትግራይ ክልል ወጣቶች መጻኢ ዕድላቸው ብሩህ እንዲሆን ለጥፋት ቡድኑ ተላላኪ ከመሆን መቆጠብ አለባቸው ብለዋል።

ዶ/ር ሙሉ፥ የጥፋት ቡድኑ ርዝራዦች በክልሉ ሕዝብ ላይ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ጉዳት እንዲደርስ እያካሄዱት ላለው ቅስቀሳ ወጣቱ ተሳታፊ ባለመሆን ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል ሲሉ ነው ጥሪ ያቀረቡት።
ወጣቱ የጥፋት ቡድኑ ርዝራዦች በክልሉ ሠላምና መረጋጋት እንዳይኖር ከውጭ አገር ሆነው የሚያስተላልፉትን የግጭት መልዕክት ዓላማ በአግባቡ ሊረዳው ይገባል ሲሉም ነው የገለፁት።

ዶ/ር ሙሉ ነጋ፥ "በአሁኑ ወቅት ወጣቱን የሚጠቅመው የሥራ ዕድል ማግኘትና ራሱን መቻል በመሆኑ ለጥፋት ተግባር ተባባሪ መሆን የለበትም" 
በክልሉ አንዳንድ አካባቢዎች የሕዝቡን ኑሮ ወደኋላ ለመመለስ እየተደረገ ያለው ያልተገባ ተግባር ትክክል አለመሆኑንም ጠቁመዋል፡፡

የጥፋት ቡድኑን ለመመለስ ማሰብና ለዚህም ጊዜ ማጥፋት ፋይዳ የሌለው ከመሆኑ በላይ ወጣቱን ስለሚጎዳ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባም ዶክተር ሙሉ አሳስበዋል።

Via Tikvah

t.me/geradomedia
7.9K viewsGashu, 18:24
Open / Comment
2021-02-13 21:23:23 በአጭር ጊዜ ውስጥ የሴት ጓደኛ እንድትኖርክ ትፈልጋለህ

በአጭር ጊዜ ውስጥ የወንድ ጓደኛ እንዲኖርሽ ትፈልጊያለሽ

ስለፍቅር ጥልቅ እውቀት እንዲኖራችሁ
OPEN የሚለውን ብቻ ይጫኑ!

OPEN
2.9K viewsGashu, 18:23
Open / Comment
2021-02-13 18:53:22
7.0K viewsGashu, edited  15:53
Open / Comment
2021-02-13 18:37:06 #ምርጫ_ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባስቀመጠው የጊዜ ሠሌዳ መሠረት ለ6ተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የተለያዩ ተግባራትን እየፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል።

ቦርዱ በማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 አንቀጽ 8 ንዑስ አንቀጽ (1) እና የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 37 ንዑስ አንቀጽ (7) እና አንቀፅ 163 ንዑስ አንቀፅ (2) ላይ በተሰጠው ሥልጣን ባወጣው የዕጩዎች ምዝገባ መመሪያ መሠረት፤ የዕጩዎችን ምዝገባ ለማከናወን የሚያስችሉትን ከክልል መስተዳድሮች እና ከከተማ መስተዳድሮች የሚጠበቁ የትብብር ግዴታዎችን ለሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ገልፆ ዝግጅቶችን እያደረገ እንደነበር ይታወቃል።

በዚህም መሰረት የክልሎች ዝግጁነት ምን እንደሚመስል ሰኞ የካቲት 01 ቀን 2013 ዓ.ም ለጋዜጠኞች በሰጠው መግለጫ አሳውቋል።

በመግለጫውም
• አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር
• ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር
• ጋምቤላ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሐረሪ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት አስፈላጊ የሆኑትን ለምርጫ ክልል እና ለዞን ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሊያገለግሉ የሚችሉ ቢሮዎችን አዘጋጅተው ለቦርዱ እንዳስታወቁ በመግለጽ፤ በጊዜ ሠሌዳው በተቀመጠው ቀን መሠረት ከየካቲት 08 እስከ የካቲት 21 ቀን 2013 ዓ.ም. የዕጩ ምዝገባ የሚከናወነው ከላይ በተጠቀሱት ክልልሎች በሚገኙ የምርጫ ክልል ቢሮዎች መሆኑን ያስታወቀ ሲሆን በቀሪዎቹ ክልሎች የክልል መስተዳድሮቹ ደግሞ አስፈላጊውን ትብብር ሲያደርጉ ምዝገባው የሚጀመርበትን ቀን ቦርዱ የሚያሳውቅ ገልፆ ነበር።

መሆኑን በዚሁ መሠረት እጩ ምዝገባ በማይጀመርባቸው ቀሪ ክልሎቹ የሚካሄዱት የዕጩዎች ምዝገባ ሂደት እንደሚከተለው ይሆናል፤
• አፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• አማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ሲዳማ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት
• ደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት እና
• ሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ከየካቲት 05 እስከ የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለዕጩዎች ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የሚጓጓዙበትና የዕጩዎች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ሥልጠና የሚሰጥበት ጊዜ ሲሆን፤ ከየካቲት 15 እስከ የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. ደግሞ የዕጩዎች ምዝገባ የሚከናወንበት ጊዜ እንዲሆን ቦርዱ ወስኗል።

(የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ)

t.me/geradomedia
5.7K viewsGashu, 15:37
Open / Comment
2021-02-13 16:03:56
ከ2 ሚሊዮን ጄሪካን በላይ የምግብ ዘይት በቁጥጥር ስር ዋለ!

በአዲስ አበባ ከተማ "ጀሞ ሚካኤል" አንበሳ ጋራዥ አካባቢ በሕገ ወጥ መንገድ የተከማቸ ከ2 ሚሊዮን ጄሪካን በላይ የምግብ ዘይት የፌዴራል ፖሊስና የላፍቶ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ከኅብረተሰቡ የደረሳቸውን ጥቆማ መነሻ በማድረግ ለ2 ሳምንታት ባደረጉት ክትትል ዛሬ በቁጥጥር ስር ውሏል። #Etv

t.me/geradomedia
5.6K viewsGashu, 13:03
Open / Comment
2021-02-12 22:13:06
"የአባሎቼ ሕይወት አደጋ ላይ ቢወድቅ መንግሥት ኃላፊነቱን ይወስዳል" - ኦፌኮ

የኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ባወጣው መግለጫ በረሃብ አድማ ላይ የሚገኙ አባሎቹ በአሁን ጊዜ የረሃብ አድማው ከረሃብ አድማ በላይ አልፎ የመታመም ደረጃ ላይ ያደረሳቸውና ሕይወታቸውም አስጊ ሁኔታ ላይ እንድወድቅ ስላደረገ መንግሥት አስቸኳይ የሕይወት ማዳን ሥራ ሠርቶ ግዴታውን እንዲወጣ ጠይቋል፡፡

ፓርቲው እነዚህ አባላት ተገቢ የሕክምና ዕርዳታ ሳያገኙ ሕይወታቸው አደጋ ላይ የሚወድቅ ከሆነ መንግሥት በሕግም ሆነ በታሪክ ተጠያቂ እንደሚሆን አሳስቧል፡፡

ኦፌኮ በመግለጫው ጨምሮም "መንግሥት በፈጠራ ክስ ያሠራቸውን አባሎቻችንና ወገኖቻችንን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ አጥብቀን እንጠይቃለን" ያለ ሲሆን፣ "መላው የኢትዮጵያ ሕዝቦች፣ በተለይም የኦሮሞ ሕዝብ፣ መላው የዓለም ኅብረተሰብ፣ በአገራችን ሕዝቦች ላይ እያንጃበበ ያለው እልቂት እንዲወገድ በተለያዩ ስልቶች መንግሥት ላይ አስፈላጊውን ጫና በማድረግ እየወሰደ ያለው የኃይል እርምጃዎችን እንዲያስቆሙ" ጠይቋል፡፡

በእስር ላይ የሚገኙት የኦፌኮ አመራር አባሎች የሆኑት አቶ ጃዋር መሐመድ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ ሌሎችም የረሃብ አድማ ማድረግ ጀምረዋል ከተባለ አስራ ሁለት ቀናት ማለፉ የሚታወቅ ነው፡፡

t.me/geradomedia
6.6K viewsGashu, 19:13
Open / Comment
2021-02-12 22:12:29 በአጭር ጊዜ ውስጥ የሴት ጓደኛ እንድትኖርክ ትፈልጋለህ

በአጭር ጊዜ ውስጥ የወንድ ጓደኛ እንዲኖርሽ ትፈልጊያለሽ

ስለፍቅር ጥልቅ እውቀት እንዲኖራችሁ
OPEN የሚለውን ብቻ ይጫኑ!

OPEN
1.4K viewsGashu, 19:12
Open / Comment
2021-02-12 21:27:39
በመተከል ዞን 120 ሽፍቶች በሠላማዊ መንገድ እጃቸውን ሰጡ!

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን ማንዱራ ወረዳ ሸፍተው የነበሩ 120 ሽፍቶች ለጸጥታ ሃይሎች እጃቸውን እንደሰጡ የክልሉ ብዙኀን መገናኛ ዘግቧል፡፡ ሽፍቶቹ ቀደም ሲል በሕወሃት ጥሪ ወደ ትግራይ ክልል ሄደው ስልጠና እንደወሰዱ ተናግረዋል ተብሏል፡፡

t.me/geradomedia
6.1K viewsGashu, 18:27
Open / Comment
2021-02-12 19:00:49
ኦነግ በቀጣዩ ምርጫ ላይ የሚያስመዘግበው እጩ ተወዳዳሪ እንደሌለው አስታወቀ!

በአቶ ዳውድ ኢብሳ የሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በመጪው አገር አቀፍ ምርጫ የሚያስመዘግው እጩ እንደሌለው አሳውቋል፡፡ ኢትዮ ኤፍ ኤም እንደዘገበው ፓርቲው በየምርጫ ክልሎች ላስመዘግብ ያሰብኳቸው እጩ ተወዳዳሪዎቼ በሙሉ በእስር ላይ ስለሚገኙ ነው የማስመዘግበው የለኝም ያለው፡፡ የፓርቲው ቃል አቀባይ አቶ በቴ ኡርጌሳ እንዳሉት ኦነግ አስፈላጊ የሚባሉ የምርጫ ዝግጅቶችን ተንቀሳቅሶ ማከናወን አልቻለም፡፡

በአሁኑ ወቅት በአመራሮቹ መካከል አለመግባባት እንዳለበት የሚነገረው ኦነግ በፓርቲው ውስጥ ለተረፈጠረው ችግር ገዢውን ፓርቲ ብልጽናን እየወቀሰም ይገኛል፡፡ ይህንኑ በሚመለከት ቃል አቀባዩ "ኦነግ የገጠመው ውስጣዊ መፈረካከስ በብልጽግና ፓርቲ ጣልቃ ገብነት የተፈጸመ ነው" ማለታቸው ተመልክቷል፡፡ ጨምረውም "ብልፅግና የራሱን ከፍተኛ አባላት ከማዕከላዊ አባልነት ሲያግድ ሁሉም በጸጋ ነው የተቀበለው፣ እኛ ግን በፓርቲያችን ውስጥ ያንን ውሳኔ ስንሰጥ ማንም ሊያከብርልን አልቻለም" ሲሉም ቅሬታቸው አሰምተዋል፡፡

ኦነግ በአዲስ አበባ ጦር ኃይሎች የሚገኘው የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሜቲ ጽሕፈት ቤቱ በፖሊስ መጠበቅ ከጀመረ ስድስት ወራት እንዳለፈው የሚናገሩት አቶ በቴ፣ "በዚህ ሁኔታ ሥራችንን መሥራት አንችልም በአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የፖርቲው ኃላፊዎችና አባላት እየታሰሩ የምናስመዘግበው እጩ የለንም" ቢሉም ይህ ግን ምርጫውን አንሳተፍም ማለታቸው እንዳልሆነ አንስተዋል፡፡

t.me/geradomedia
6.1K viewsGashu, 16:00
Open / Comment