🔥 Burn Fat Fast. Discover How! 💪

ገራዶ ሚዲያ

Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Logo of telegram channel geradomedia — ገራዶ ሚዲያ
Channel address: @geradomedia
Categories: News
Language: English
Subscribers: 679
Description from channel

🔸ሁሉን አቀፍ የመረጃ ምንጭ!🔸
✍ ፃፉልን @geradomediabot
fb.com/geradomedia
twitter.com/geradomedia

Ratings & Reviews

3.00

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

1

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 54

2021-02-09 10:29:19
ሱዳን አዲስ ካቢኔ አዋቀረች!

በሚኒስትር ደረጃ ያሉ የካቢኔ አባሎቻቸውን የበተኑት የሱዳኑ ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሃምዶክ አዲስ ካቢኔ አዋቀሩ፡፡

ሃምዶክ ካቢኔው ባለፉት ሶስት ወራት በፓርቲዎች መካከል ሲደረግ በነበረው ምክክር እና ስምምነት ሃገሪቱን ከውድቀት ለመታደግ በሚያስችል መልኩ ወቅታዊ ቀጣናዊ ስጋቶችን ታሳቢ አድርጎ መዋቀሩን ገልጸዋል፡፡

ችግሮች ቢኖሩም እንኳን ካቢኔው ሲዋቀር ሃገራዊ መልክ እንዲኖረው ሆኖ መዋቀሩን ነው ሃምዶክ የተናገሩት፡፡

በካቢኔው ለውጥን በማቀጣጠል ድርሻ እንዳላቸው የሚነገርላቸው አካላት፣ ወታደራዊ ቡድኖች እና የሰላም አጋሮች ተካተዋል፡፡

ይህ ካቢኔውን በልዩነቶች እንዲፈተን ሊያደርግ ይችላል፡፡

ሆኖም ከችግሮች የጸዳና የተላቀቀ ህብረት ሊኖር አይችልምና ለሃገሪቱ ደህንነት የሚበጅ እውነተኛ ትብብር እንዲኖር እንሰራለን ሲሉ ቃል ገብተዋል ሃምዶክ፡፡

የሽግግር ጊዜውን በወጉ የሚመራ ህግ አውጪ ሸንጎን በቶሎ ለማዋቀር በፍጥነት ሊሰራ እንደሚገባም ነው የተናገሩት፡፡

እንደ ሃገሪቱ ዜና አገልግሎት ዘገባ ከሆነ ሸንጎው እ.ኤ.አ እስከ መጪው የካቲት 25 እንዲዋቀር እቅድ ተይዞለታል፡፡

Via AlAin Amharic

t.me/geradomedia
5.3K viewsGashu, 07:29
Open / Comment
2021-02-08 22:11:01
#NEBE2013

ለመጭው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ የምርጫ ክልል እና የዞን ማስተባበሪያ ቢሮዎችን አዘጋጅተው ለቦርዱ ባላስረከቡ የክልል መስተዳድሮች በተቀመጠው የጊዜ መርሃ ግብር የዕጩዎች ምዝገባ እንደማያካሂድ ዛሬ ለመገናኛ ብዙኀን በላከው መግለጫ አስታውቋል። እስካሁን የክልል እና ዞን የምርጫ ቢሮዎችን ባላሳወቁት አማራ፣ አፋር፣ ሱማሌ፣ ደቡብ እና ሲዳማ ክልሎች፣ የዕጩዎች ምዝገባ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና እና የምርጫ ቁሳቁሶች ስርጭት ማከናወን አልቻልኩም- ብሏል ቦርዱ። በተጠቀሱት ክልሎች ሌላ ጊዜ የዕጩዎች ምዝገባ እንዲደረግ፣ እስከ የካቲት 5 ቢሮዎችን እንዲያሳውቁም አሳስቧል።

t.me/geradomedia
5.8K viewsGashu, 19:11
Open / Comment
2021-02-08 22:09:35 በአጭር ጊዜ ውስጥ የሴት ጓደኛ እንድትኖርክ ትፈልጋለህ

በአጭር ጊዜ ውስጥ የወንድ ጓደኛ እንዲኖርሽ ትፈልጊያለሽ

ስለፍቅር ጥልቅ እውቀት እንዲኖራችሁ
OPEN የሚለውን ብቻ ይጫኑ!

OPEN
1.4K viewsGashu, 19:09
Open / Comment
2021-02-08 20:19:09
#Ethiotelecom

በሰሜን ሪጅን የቴሌኮም መሠረተ ልማት ጥገና እና አገልግሎትን የተመለከተ ወቅታዊ መረጃን በምስሉ ላይ መመልከት ትችላላችሁ!

t.me/geradomedia
5.6K viewsGashu, 17:19
Open / Comment
2021-02-08 18:52:18
የነ አቶ ጃዋርና በቀለ ገርባ የረሃብ አድማ....

እነ አቶ ጃዋር መሐመድ፣ በቀለ ገርባ፣ ሐምዛ አዳነ እና ሸምሰዲን ጠሃ የረሃብ አድማ ማድረግ ከጀመሩ 12 ቀናት እንደሆናቸው ከOromo Political Prisoners Defense Team የተገኘው መረጃ ያሳያል።

ቢቢሲ እንዳስነበበው ከሆነ ደግሞ ከአራቱ በተጨማሪም በእነ አቶ ጃዋር መሐመድ የክስ መዝገብ ሥር የሚገኙ ተከሳሾች የረሃብ አድማውን ተቀላቅለዋል።

ተከሳሾቹ የአቶ ጃዋር መሐመድ ጠባቂዎች እና የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትዎርክ ጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ ሲሆኑ አድማውን ከተቀላቀሉ 6 ቀናት አልፏቸዋል።

ይህን ያሳወቁት ከእነ አቶ ጃዋር መሐመድ ጠበቆች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ምስጋኑ ሙለታ ናቸው።

እነ አቶ ጃዋር መሐመድን ትናንት ጠዋት መጎብኘታቸውን የሚያስረዱት ጠበቃው፥ "ትናንት 11ኛ ቀናቸው ነበር። በጣም ተዳክመዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የአቶ በቀለ ገርባ ባለቤት ወ/ሮ ሃና ረጋሳ ለቢቢሲ፤ እነ አቶ በቀለ አሁንም በረሃብ አድማ ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል።

የጋዜጠኛ መለሰ ዲሪብሳ ባለቤት ታደለች መርጋ፥ ባለቤቷ የረሃብ አድማውን መቀላቀሉን እና ለመጠየቅ ይዛለት የምትሄደውን ምግብ አልቀበልም እያላት መሆኑን ገልጻለች።

ጠበቃ አቶ ሙለታ፥ "አንዳንዶቹ በሰው ድጋፍ ነው ከክፍላቸው የሚወጡት። በተለየ ደግሞ ዘግይተው የረሃብ አድማውን የተቀላቀሉት በጣም ከብዷቸዋል" ሲሉ ተናግረዋል።

የእነ አቶ ጃዋር ሃኪሞች "ምርመራ ካደረጉላቸው በኋላ ውሃ ካልወሰዱ አንዳንድ የሰውነት አካላቸው ሥራ ሊያቆም እንደሚችል ከነገሯቸው በኋላ ነው በግድ ውሃ እየወሰዱ ያሉት። ምግብ የሚባል ነገር አፋቸው ጋር እየደረሰ አይደለም" ሲሉ አስረድተዋል።

Via BBC & Oromo Political Prisoners Defense Team #tikvah

t.me/geradomedia
5.1K viewsGashu, edited  15:52
Open / Comment
2021-02-08 16:02:24
34ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ.....

- ጉባኤው ለሁለት ቀናት ሲካሄድ ቆይቶ ትላንት ምሽት ተጠናቋል።

- በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ጉባኤው በቪድዮ ኮንፈረንስ ነው የተካሄደው።

- "የአፍሪካን ባህል፣ ኪነት፣ ሙዚቃ ፣ ቋንቋና ትውፊት ይዘን አፍሪካን ወደምንፈልግበት እናደርሳለን" የሚል መሪ ቃል ነበረው።

- የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ፕሬዜዳንት ፌሌክስ ቺሲኬዲ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

- አዲሱ ሊቀመንበር አዲስ አበባ ተገኘተው የAU ጉባኤ አዳራሽ ውስጥ ከቀድሞ ሊቀመንበር የደቡብ አፍሪካው ፕሬዜዳንት ራማፎሳ (እሳቸው ቨርቿል) ሆነው ርክክብ አድርገዋል።

- ከቻድ ሙሳ ፋኪ እንደገና የAU ዋና ኮሚሽነር ሆነው ተመርጠዋል። ምክትል ኮሚሽነር የሩዋንዳዋ ዶክተር ሞኒክ Nsanzabaganwa ሆነው ተመርጠዋል።

- የአፍሪካ ሰላም ጉዳይ፣ የኢኮኖሚ ውህደት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር በአፍሪካ ማስፈን ሌሎች አፍሪካን እየተፈታተኑ ያሉ ችግሮችን የሚያነሱ አጀንዳዎች ነበሩ። በዋነኝነት ኮቪድ-19 ወረርሽኝ መዋጋት፣ ክትባት ለሁሉም ማዳረስ የሚሉት ሃሳቦች ተነስተውበታል።

Via Ambassador Dina Mufti #Tikvah

t.me/geradomedia
5.0K viewsGashu, edited  13:02
Open / Comment
2021-02-08 14:30:22
የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ልዑክ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየትና ድጋፍ ለማድረግ ወደ ትግራይ ክልል አቀና!

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎችንና መማክርትን ያካተተ ልዑክ በወቅታዊ ሁኔታ ላይ ለመወያየትና ድጋፍ ለማድረግ ወደ ትግራይ ክልል ማቅናቱን የጉባኤው ዋና ጸሃፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ገለጹ።

ከዛሬ ጀምሮ ለሦስት ቀናት የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የበላይ ጠባቂ አባቶችን፣ የሀገር ሽማግሌዎች መማክርትን ያካተተ ልዑክ ወደ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ ማቅናቱ ነው የተጠቀሰው።

ልዑኩ በሚኖረው ቆይታ በክልሉ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከህብረተሰቡና ከባለድርሻ አካላት ጋር እንደሚወያይም ነው የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ጸሐፊው ለኢዜአ ገልጸዋል።

ልዑኩ በሚኖረው ቆይታ በተካሄደው የሕግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ያጋጠሙ ችግሮችንና፣ በተለይም በቤተ እምነቶች ላይ በደረሰው ጉዳት ዙሪያ እንደሚመክር ተናግረዋል።

በተጨማሪም ልዑኩ በቀጣይ ምን መሠራት እንዳለበት ከአከባቢው የእምነት አባቶች፣የሀገር ሽማግሌዎች፣ እንዲሁም ከመንግሥት እና ከጸጥታ አካላት ጋር ምክክር ይደረጋል ብለዋል።

የጉባኤው አባል የሆኑት የሐይማኖት ተቋማትም የድጋፍ ስራዎችን እንደሚያከናውኑና በአሜሪካ የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አገረ ስብከቶችን የሚመሩ ሊቃነ ጳጳሳት በኦን ላይን ያሰባሰቡት ድጋፍም ለህበረተሰቡ እንደሚለገስ ዋና ጸሐፊው መግለፃቸውን ኢዜአ ዘግቧል።

t.me/geradomedia
4.7K viewsGashu, 11:30
Open / Comment
2021-02-08 13:46:24
ኢትዮጵያ በመጭዎቹ ዓመታት ህዳሴ ግድብን ጨምሮ በሰባት ውሀማ ስፍራዎች የውሀ ትራንስፖርት አገልግሎት እንደምታስጀምር አስታወቀች።

ሀገሪቷ አሁን ያሉት እንዳለ ሆኖ ተጨማሪ የመሰረተ ልማት ማስፋፋት ይሰራሉ ቀድመው ስራ የጀመሩት ደግሞ በተሻለ ቴክኖሎጂ ወደ ስራ እንዲገቡ ይደረጋል ተብሏል።

በ10 አመቱ መሪ የትራንስፖርት የልማት እቅድ ውስጥ ከተቀመጡ ጉዳዮች መካከል የውሀ ትራንስፖርት መሰረተ ልማት ይገኝበታል፡፡

በዚህም በጣና ሀይቅ፣ ባሮ ወንዝ፣ አባያ፣ ጫሞ፣ ተከዜ፣ ህዳሴ ግድብ እና በጊቤ የውሀ ትራንስፖርት መሰረተ ልማት ለማልማት ታቅዶ ስራ መጀመሩ ተገልጿል፡፡

የትራንስፖርት ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር የኋላሸት ጀመረ ለኢትዮ ኤፍ ኤም እንደተናገሩት በ10 ዓመት የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ የልማት ዕቅድ የዉሃ ትራንስፖርት ልዩ ትኩረት ተሰጥቷል።

የዉሃ ትራንስፖርት ደህንነቱ የተጠበቀና በሚፈለገዉ ደረጃ በሀገራችን ያለዉን ለዉሃ ትራንስፖርት አገልግሎት አመቺ የሆኑ ወንዞችና ሃይቆች በአግባቡ በመጠቀም ለህዝብና ለጭነት ትራንስፖርት አመቺ ሆነው ይለማሉ ተብሏል፡፡

የውሀ ትራንስፖርት አማራጭ የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ሆኖ እንዲያገለግል እንዲሁም ለመዝናኛና ለቱሪስት መስህብነትም እንዲያገለግሉ መሰረተ ልማቶች በስፋት ይለማሉ ተብሏል፡፡

Via Ethio FM

t.me/geradomedia
5.0K viewsGashu, 10:46
Open / Comment
2021-02-07 18:29:30
የፕ/ት ሳህለወርቅ ዘውዴ የመቐለ ጉብኝት...

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በትግራይ ክልል መቐለ ከተማ የተለያዩ አካባቢዎችን ጎብኝተዋል። በጉብኝታቸውም በመቐለ ከተማ የሚገኙትን የዓይደር ስፔሻላይዥድ ሆስፒታል፣ የፌደራል መንግስት እህል ማከማቻ ማዕከላዊ መጋዘን እና በትግራይ ክልል በተካሄደው የህግ ማስከበር ዘመቻ ወቅት ከተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለው በከተማዋ የሚገኙ ተፈናቃዮችን አይተዋል፡፡

ፕሬዘዳንቷ ከመቐለ የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎች ጋርም ውይይት አካሂደዋል። በውይይቱም የአገር ሽማግሌዎች በአሁኑ ወቅት በትግራይ ክልል የተንሰራፋው የሥራ አጥነት ችግር እንዲፈታ፣ ከመንግስት ቢሮዎች የተዘረፉ ቁሳቁሶች ተሟልተው በተጠናከረ መልኩ ስራ እንዲጀምሩ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

በትግራይ በአሁኑ ወቅት በዋናነት ለሰላም እና ለጤና ቅድሚያ ተሰጥቶ መሰራት እንዳለበትም አመልክተዋል፡፡ በተጨማሪም መንግስት እያቀረበ ያለውን የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት አጠናክሮ እንዲቀጥል አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በሰጡት ምላሽም ትግራይን ወደቀደመው ሰላም ለመመለስ መንግስት በቁርጠኝነት እየሰራ ይገኛል፡፡ በትግራይ ክልል መንግስት ህዝብ አብሮ የሚኖርበትንና የሚደጋገፍበትን ስርዓት በመገንባት ላይ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በትግራይ ክልል ያሉ የሕዝብ ጥቄዎች በአፋጣኝ እንዲፈቱ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው ክልሉን መልሶ በማደራጀት ሂደት ውስጥ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር እንደሚያስፈልግ አሳስበዋል።

ፕሬዚዳንቷ በመቐለ ያደረጉትን ጉብኝት በማጠናቀቅ ወደ አዲስ አበባ መመለሳቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

t.me/geradomedia
5.9K viewsGashu, 15:29
Open / Comment
2021-02-07 18:29:24 በአጭር ጊዜ ውስጥ የሴት ጓደኛ እንድትኖርክ ትፈልጋለህ

በአጭር ጊዜ ውስጥ የወንድ ጓደኛ እንዲኖርሽ ትፈልጊያለሽ

ስለፍቅር ጥልቅ እውቀት እንዲኖራችሁ
OPEN የሚለውን ብቻ ይጫኑ!

OPEN
2.4K viewsGashu, 15:29
Open / Comment