Get Mystery Box with random crypto!

በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ

Logo of telegram channel bewketuseyoum19 — በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ
Logo of telegram channel bewketuseyoum19 — በእውቀቱ ሥዩም እና ሥነ-ፅሁፍ
Channel address: @bewketuseyoum19
Categories: Courses & guides
Language: English
Subscribers: 128.65K
Description from channel

➲የበእውቀቱ ስዩም ፈገግታም እውቀትም የሚሰጡ ወጎች ፣ ግጥምች እና የተለያዩ ፀሀፊዎች የስነጽሑፍ ስራዎች የሚቀርብበት ቻናላችንን ይቀላቀሉ፡፡
@bewketuseyoum19
Buy ads: https://telega.io/c/bewketuseyoum19
For your comment,feedback and promotion @Bewketuseyoum2bot
Thank you!

Ratings & Reviews

1.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

0

2 stars

1

1 stars

1


The latest Messages 123

2022-05-31 21:09:08
ጦቢያ ላይ የምታውቁት ተስፋሁን (ፍራሽ አዳሽ) የተቀነጫጨቡ ቀልዶችን ለማግኘት ተመራጭ ቻናል አቅርበንላችኋል አሁኑኑ JOIN በማለት መቀላቀል ይቻላል።
2.3K viewsENFALOTE‌‌ ° , 18:09
Open / Comment
2022-05-31 20:48:49 ለካስ ቀን ይመጣል
ከፊሊሞና

ረቂቅ ቃላትን ላንተ ሰባጥሬ
መፅሀፍ ቅዱሱን ከፊቴ ደንቅሬ
ከበራፍህ ቆሜ ፀሎት አድርሻለው
ስጋና ደምህን በአፌ ቀምሻለው
ሀጢአቴን እንዳብስ ላንተ ሰግጃለው ።
ፀበል ተጠምቄ ትዕዛዝን አክብሬ
ለእምነቴ ፅኑ ታምኜ ለክሬ
ቆሜ አለው ከደጅህ ምላሽ እንድትሰጠኝ
ላደረስኩት ፀሎት መልሱን እንድትነግረኝ።

ፀሎቴ ደረሰህ ምላሽ ስጠኝ ጌታ
ሞት እንዳይቀድመኝ አለምን ሳልረታ
ግን
ለሁሉም ጊዜ አለው
ለካስ ቀን ይመጣል
ፀሎቴም ይደርሳል ።

አሜን ።

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.2K viewsAbela, 17:48
Open / Comment
2022-05-31 17:39:32 የፍቅር መድረሻው!
(አኑ)

ሂድ ስትለው መጣ፣
ውረድ ሲባል ወጣ፣
ውጣ ሲባል ሲወርድ፣
አንዴ እሷን ሲጠላ ፣ አንዴ ደግሞ ሲወድ፣
ከራሱ ተጣልቶ፣
ከራሱ ተኳርፎ፣
ነብሱን ይረግማታል በአንዲት ሴት ተለክፎ

(ያቺ ሴት)

የሆነ ዘመን ላይ ፍቅረኛው ነበረች
በፍቅሩ የከነፈች፣
ስለሱ የምትኖር፣ ስለሱ የምትሞት!
እሱም የሚያፈቅራት
ከጎና ማይጠፋ
ፍቅር እንደማግኔት ከሷ ጋር አጣብቆት!
አንድ'ዜ በሀይቅ
አንድ'ዜ በየብሱ
አንድ'ዜ በአየር
ፍቅርን ሸክፈው ሲንሳፈፉ ነበር።

(ዛሬ)

ተጣልተው
ተኳርፈው
ደግሞም ተለያየተው
አንድ ፍቅራቸውን ሁለት ቦታ ከፍለው
ጎጆውን አፍርሰው
ተነጣጥለው አሉ
ትላንትን ታቅፈው እንዲኹ ይኖራሉ።

(እሱ)

ጎዳና ዳር ካለ አንድ ካፌ ገብቶ
ለካፌ አሳላፊው ፣ አዞ ማኪያቶ
( ሁለት ነው ያዘዘው)
አንደኛው ለራሱ
ሁለተኛው ደግሞ ለሄደች ፍቅሩ
እርግጥ ነው የለችም
በምዕናብ ሊያኖራት ከባዶ ወንበሩ
(እንዲኽ ነው ሀሳቡ)

ትዕዛዙ እስኪመጣ
ጋዜጣ ያነባል
የጋዜጣው ርዕስ
ጥያቄ ይጠይቃል

(ጥያቄው)
ከአላህ እና ከእግዜር የቱ ነው ትክክል?
ከርዕሱ በታች
የቄስና የሼኽ የፈገግታ ምስል ፣

(እዚህ ጋር)

ቄሱም ሆነ ሼኹ
የፃፉትን ፅህፈት፣
የሰበኩት ስብከት፣
ካነበበ ኋላ ደረሰ ከእውነት!

(እውነቱ)

የቄሱም የሼኹም
የኣላህም የእግዜሩም
ቃሎች ሲመረመር
ፍቅር ነው መነሻው፣ ፍቅር ነው መድረሻው፣
ከፍቅር ለራቀ
የይቅርታ ቃል ነው መምጫ መመለሻው፣

( ያዘዘው ማኪያቶ ከመጣ ቆይቷል
ጋዜጣ ሲያነብ ረስቶት ቀዝቅዟል)

ሳይጠጣው ተነሳ
ጋዜጣውን ይዞ መንገዱን ጀመረ
ሚጓዝበት መንገድ
ማይሽር ፣ የማይጠፋ
ከአንዲት ፍቅሩ ጋራ ትዝታ ነበረ።
እርምጃው ፈጠነ
ይሄዳል ፣ ይሄዳል ፣ ይሄዳል ፣ ይሄዳል
ፍቅሩ ቤት ደረሰ ፣
በሯን ደበደበ፣
እየሮጠች ወጣች፣
የበፊት ህይወቷ ፊትለፊቷ ቆሟል
የምትለው ጠፋት
ፍርሀት ነብሷን ዋጣት


ሱ...

ተንበርክኳል
እግሯ ስር ተገኝቷል
በስስት ፣ በፍቅር
ሽቅብ አይኗን ያያል
ይቅርታ የሚል ቃል
ከአንደበቱ ይፈልቃል




አለቀሰች
አይኗን እንባ ወረሰው፣
አካላቷን ሙሉ ደስታ አንቀጠቀጠው፣

ተነሳ አቀፈቹ
ሲያያት ሳመቹ









አለች
እየሳቀች

ጋዜጣውን አየ

ፍቅር ነው መነሻው ፣ ፍቅር ነው መድረሻው ፣
ከፍቅር ለራቀ
የይቅርታ ቃል ነው መምጫ መመለሻው፣

ይኽን አስታውሶ
ፊቱን ብርሀን ሞላው።


@anu_yesua

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
3.8K viewsAbela, 14:39
Open / Comment
2022-05-31 14:01:57 ተክለሃይማኖት ከፍተኛ ክሊኒክ !

በታቦት እንዳንምል...ፃድቃን እንዳንጠራ
አልኮል ሲሰለጥን...እውቀት ሲንጠራራ
ሆኑትና አረፉት...በተራ በተራ
ቅድስት ማርያም ኮሌጅ...ቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ

በሙሉቀን ሰ•

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.4K viewsAbela, 11:01
Open / Comment
2022-05-31 06:30:56
• አስደሳች ዜና • !

•ማንኛውም አይነት አዲስ የአማሪኛ ዘፈኖችን የሚገኝበት ምርጥ ቻናል ነው
ከ 140,000 በላይ ተከታዮች የሉት ን ቻናል ይቀላቀሉ

https://t.me/joinchat/7b8Hl8TeX1xiMGQ0
https://t.me/joinchat/7b8Hl8TeX1xiMGQ0
70 viewsENFALOTE‌‌ ° , 03:30
Open / Comment
2022-05-30 23:24:08
ለ Pp የሚሆን ጥቅስ አጥተው ያውቃሉ?
ወይስ ለፍቅርኛዎ የሚልኩት የፍቅር መልዕክት ይፈለጋሉ? ተቀላቀሉን
746 viewsENFALOTE‌‌ ° , 20:24
Open / Comment
2022-05-30 10:12:42 አንዳንዴያችን

የኔ እና እሷ አንዳንዴ
ስትሄድ በመንገዷ ስሄድ በመንገዴ
ልትፈልገኝ ስትመጣ ልፈልጋት ስሄድ
ለፍለጋ እንወጣለን በሁለት ልዩ መንገድ
እሷም ልቤን ስታሳድድ እኔም ልቧን ሳሳድደው
እሷው ትመጣለች እኔው ለምሄደው
ጀርባዬን ስታየው ጀርባዬ ይያት እንጂ
አላያት አታየኝ
ላንገናኝ........
ፈላጊዬ ሆናለች ፈላጊዋ ስለሆንኩኝ
አንዳንዴ......
ለየቅል ጉዟችን ፍለጋ ስንማስል
ለሷ ይነጋና ለኔ ግን ይመሻል
ቀኑ ለሷ ሆኖ ሌቱ ለኔ ይሆናል
አንዳንዴያችን ቀጥሎ.....
ላሜ ልትሆነኝ ፍቅር ልታስልበኝ
ወደ እኔ ስትመጣ
እኔዋ ጥጃዋም ፍቅር ወተት ልፈልግ
ከቤቴ ስወጣ
ልትፈልገኝ ስትወጣ ልፈልጋት እንደሄድኩኝ
ቤቴ ትደርሳለች ቤቷ እንደደረስኩኝ
የኔ እና እሷ እንዳንዴ......
ስትሄድ በመንገዷ ስሄድ በመንገዴ
አልተገናኘንም አልታደልንም አንዴ
ግጥምጥሞሽ ወዶን ሰምሮም አንገናኝ
ልትፈልገኝ ስትመጣ ልፈልጋት ስለሄድኩኝ።

ቴዲ ጌትነት።
ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
366 viewsAbela, 07:12
Open / Comment
2022-05-29 20:37:16 ልክ እንደ እነኛ
አላፊ ና አግዳሚ
ሳይለዩ ሚመቱ ሰው ከመጋኛ
ከአደባባይ ቆመው እጅ እየሰደዱ
እንዴት ነው ሚመታው ሰውን የወደዱ
የኔን ግን የኔን ግን
ካየሽ እንደው እጄ እንኳ ተነስቶ
ፈራ ተባ ሳቲ ላስቀርሽ በፎቶ
።።።።።።።።።።።።።።።።።።

ግልባጩ እሷ ዘንድ አለ

#የወሎ_ቆንጆ

ሳሙኤል አለሙ

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
2.2K viewsAbela, 17:37
Open / Comment
2022-05-29 13:38:58 አዙሪት
።።።።።

አንዳንዴ...
እንዲህ አስባለሁ...
አይሁድ ክርስቶስን...
ባይወጋ ባይገርፈው...
ተለቀሀል ብሎ...
በርባንን ባያልፈው...
አስራ ሁለት ዙር...
ሰንሰል አሰርቶ...
ከገነት ደጃፍ ላይ...
ሚካኤልን ጠርቶ...
በርባንን ጠፍንጎ...
በቸነከረልኝ ምነበር እላለሁ...
ለሞተልኝ መሲህ...
ጥብቅና እቆማለሁ...

------------------------------

ግን'ኮ ማርያምን...
አዙሪት አይደለም...
ጠምቆኝ ብሰክር ነው...
የሰውነት ቀለም...
ማርያም ባታለቅስ...
መስቀሉን ታክካ...
በወጉ በጦምን...
ቀርቶብን ፋሲካ...
እግር ማጠብ ትተን...
እግር ባልቆረጥን...
ወዳጅ መሆን ቢያቅት...
ሰው ስመን ባልሸጥን...

----------------------------

ዘንባባ ባንቀጥፍ...
ለመልካም መካሪ...
መቆለፍ ከበደን...
የአመንዝራን ሱሪ....
ከፈትነው...
ዚፑን ወለል አርገን...
የደቂቃ ግልቢያ ...
ግለቱ በልጦብን ከገነት ወጋገን...
ከንፈር ተዘላዘልን...
ገላ ተቋደስን...
ዳሌ ስንጨመድድ...
የመሲሁን ቅኔ እየደመሰሰሰን
ዘለልን በአልጋው ላይ...
ሾርን በወለሉ...
ፋፋን በእንቡጦች ደም...
ሳጥናኤል ተዝናና
ስራው በመቅለሉ
በርባን ቢሆን ሟቹ...
ወንበዴው ቢደማ...
ይጣፍጠን ይሆን?
ሰው የመሆን ዜማ?
ጨለማው ባይነግስ...
ቀን በቀንነቱ ብርሀን ቢሰፍበት...
የቤተመቅደስ ጨርቅ ቁልቁል ባይመተር ዕድሜ ሰጥቶት ቢቀር
እንዲያ እንዳማረበት...
ለገረፉት ባይጮህ...
ምህረትን ከአባቱ...
ሰው ሰው እንሸት ይሆን?
በበርባን ስቅለቱ?
ደቅሲዎስ ገላውን
ገንዞ ባይቀብረው
የትንሳኤው ዜና
አይሁድን ባይገርመው
በርባን ቢሞት ኖሮ
በክርስቶስ ቦታ
እኔ እነሳ ይሆን
የማታ የማታ?

በማዕዶት ያየህ
(ሀሳቡ ከሌላ የተወሰደ)

13/08/2014 ዓ.ም.

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.0K viewsAbela, 10:38
Open / Comment
2022-05-29 11:53:11 እንዲሁ ስከተልሽ

እውነት

እግዜሩን አላውቀው
ከደጁ አልቀርበው
እንደሰው ሄጄ መሬቱን አልስመው
ወይ ፀሎት አላደርስ
ቅዳሴ አላስቀድስ
አባቴ ሆይ ማረኝ ብዬ እኔ አላለቅስ
ዳዊቱን ስደግም መች እኔ እገኛለሁ
ማህሌት ሰአታቱን በእንቅልፍ አልፋለሁ
እንዲህ እንዲህ እያልሁ እርሱን ረስቼ
መጠጥ ጭፈራ ቤት ተስቤ ገብቼ
አንድ ቀን አየሁሽ ከቅዱሱ ስፍራ
ነጠላን ጣል አ'ርገሽ ከምዕመናን ጋራ
አምላኬ ተመስገን
በደሌንም ማረኝ ስትይ ሰማሁሽ
ቀልቤን ገዛሽና እንዲሁ ተከተልኩሽ
አንቺ ካለሽበት
በደመነብስ ስቀርብ ራሴን አየሁት
ለእልፍ አእላፍ ዘመን ደርሶ የማያውቀውን
ከእግዜሩ ግቢ እግሬን አገኘሁት

ስብሀት ለአብ ለወልድ ለመንፈስቅዱስ ብዬ ተሳለምኩኝ
አንቺ እንዳደረግሺው
ከበሩ ሰግጄ መሬቱንም ሳምኩኝ
ካጠገብሽ ሆኜ ስብከቱን ሰማሁኝ
ስትወጪውም ከኋላሽ ተከትዬሽ ወጣሁ
ስምሽን ጠይቄ እንደምንም ተግባባሁ
ምስጋና ለፍቅርሽ
ቀና ብዬ አምላክን የ'ኔ አድርጋት አልሁት
ደግሜ ደግሜ ደግሜ ጠየቅሁት
እሱም አልጨከነ እንደኔ አይደለም
ለፀሎት ጥያቄ ምላሽ አልነፈገም
ወድጄሽ ነውና
አንቺን ፍለጋ እግርሽን ስከተል
አትጠፊም እና ቤተ ክርስቲያን ስውል
አጠገብሽ ቆሜ
ውዳሴን ከፍቼ ስቡህኒ ብለው
ዳዊትን ደግሜ
አምላኬ ሆይ ማረኝ ብዬ ብማፀነው
የ'ኔ እንዲያደርግሽ ማህሌቱን ብቆም
ፍቅርን ፍለጋ
ልብሽ አሸፍቶኝ ገዳማቱን ብዞር
በፀሎት በስግደት በፆም ውዬ ባድር
ንስሀ ገብቼ በይቅርታ ወደቅኩ
ከረሳሁት ጌታ በሂደት ተታረቅኩ
ለካ በምክንያት ነው አንቺን ያስወደደኝ
ባ'ንቺ ተማርኬ ከቤቱ እንድገኝ
ልብሽ አሸፍቶኝ እንዲሁ ስከተልሽ
ከተጣላሁት ቤት
ከአባቴ እርስት ዞሬ ገባሁልሽ።

ሰላም ላንተይሁን

ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!
@bewketuseyoum19
@bewketuseyoum19
4.1K viewsAbela, 08:53
Open / Comment