Get Mystery Box with random crypto!

🌺 ለስኬታማ ቤተሰብ 🌺

Logo of telegram channel nesiha_ouserya — 🌺 ለስኬታማ ቤተሰብ 🌺
Logo of telegram channel nesiha_ouserya — 🌺 ለስኬታማ ቤተሰብ 🌺
Channel address: @nesiha_ouserya
Categories: Education
Language: English
Country: Ethiopia
Subscribers: 2.48K
Description from channel

ለስኬታማ ቤተሰብ - نحو الأسرة الناجحة
ቤታችንን ኢሰላማዊ በማድረግ ትዉልድን እናድን!
ስለ ቻናላችን ያሎትን ሀሳብና አስተያየት
በ @nesiha_ouserya_Bot ይላኩልን!
እናመሰግናለን!
@nesiha_ouserya

Ratings & Reviews

2.50

2 reviews

Reviews can be left only by registered users. All reviews are moderated by admins.

5 stars

0

4 stars

0

3 stars

1

2 stars

1

1 stars

0


The latest Messages 17

2021-01-19 20:12:11


ሒጃብን እንዴት እንረዳው? ➌
••●••

●እህቴ_ሆይ! ሂጃብ ነፃነትን አይነጥቅም፡፡ ለምድራዊ ህይወትሽ ስኬት ቁልፍ የሆነውን የአዕምሮ ነፃነት አጎናፅፎሽ የውድቀት በር ለሚከፍተው የስሜት ነፃነት ልጓም ያበጅለታል እንጂ፡፡
••●••
●ሂጃብ ለመጪው ዘላለማዊ ህይወት የማይነጥፍ ስንቅ ነው፡፡ ፍጡራንን ሁሉ ካለመኖር ጨለማ ወደ መኖር ብርሀን አስገኚ የሆነው አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ)በሴት ምዕመናን ላይ ያለው መብት ነው፡፡ እርቃን እንደ ስልጣኔ፣ ሀፍረተ ቢስነት እንደ እድገት በተቆጠረበት ዘመን ከልብስ ያንቺው ሂጃብ እንጂ ምን የቀረ አለ?
••●••
●#እህት_አለም! የሰው ልጅ አላህን በብቸኝነት የማምለኩ መገለጫ ሁሉንም የህይወት ጉዳዮችን አላህ በሚወደው መልኩ ማከናወኑ፣ እምነቱን፣ ንግግሩን ተግባሩን፣ ህይወቱንና ውሎውን ከአላህ ትዕዛዛትና መመሪያ አኳያ መቅረፁ ነው፡፡
••●••
●ሙስሊም የሚፈፅመው ቃል ኪዳን፣ የሚያከብረው መርህ፣ የሚከተለው ጎዳና አለው፡፡ ይህ ለአላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ)) ትዕዛዛት ተገዢነቱ የእምነቱ መገለጫ ብቻ ሳይሆን የእምነቱ መሰረት ነው ፡፡
••●••
●የህይወቱን ልጓም የጌታው ቃልና የአላህ መልዕክተኛ (ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም) ይመሩት ዘንድ በፍቃዱና በምርጫው አሳልፎ ሰጥቷል።
••●••
●ይህ ፍቃዳዊ ምርጫ የነፃነት ቀንዲል ነው፡፡ ለፍጡራን ከማደር፣ ከመንበርከክና ከመተናነስ፣ የሰውን ልጅ ባሪያ ከሚያደርጉ፣ ነፃነቱን ከሚጋፉ አስተሳሰቦችም ሆነ ተግባራት የሚታደገው የምጥቀት ጎዳና ነው፡፡
•• ● ••

#ሒጃብ

3.4K viewsedited  17:12
Open / Comment
2021-01-19 12:45:32 ዛሬ ላይ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ በጣም የሚያስፈልገው...

መልካም አርዐያ

ልጆችን መልካም አርአያ በመሆን ማነፅ ጠቃሚ፣ ለውጤታማነት የቀረበና በህብረተሰቡ ዘንድም ተፅዕኖ ፈጣሪ የሆነ የተርቢያ ዘዴ ነው።

በተርቢያ(የልጆች አስተዳደግ) ላይ መጽሐፍ መፃፍ ፣ማውራት ወይም ሥርዓተ-ትምህርትን ማዘጋጀት ቀላል ነው ፣ ነገር ግን ሰዎች በምድር ላይ ወደሚያዩት ተጨባጭ እውነታ ካልተለወጠ በስተቀር ይህ ሁሉ በወረቀት ላይ ያለ ቀለም ወይም ባዶ ቃላት ይሆናል።

በዚህ ረገድ ሰለፎች (ቀደምቶች) የነበራቸው ግንዛቤ ጥልቅ በመሆኑ ለትውልድ አስተማሪዎች እንዲህ ይሉ ነበር ፡፡

"ልጄን ከምታስተካክልበት የመጀመሪያው ነገር እራስህን ማስተካከል ይሁን።ዓይኖቻቸው ከዓይኖችህ ጋር የተሳሰሩ ናቸው ፣ በነሱ ዘንድ መልካም ማለት አንተ ያደረግከው ነገር ነው፣ ለእነሱም አስቀያሚው አንተ የተውከው ነው።"

ሰዎችን በመለወጥ (በተርቢያ) ውስጥ በጣም ዉጤታማ ከሚያደርጉ ነገሮች ከሙረቢው (ከአስተማሪው) ተግባርን ማየት እና ቃላቶች ወደ ድርጊቶች ሲለወጡ ማየት ነው።

በአብዛኛው ሰዎች የሚማሩት በሚሰሙት ሳይሆን በሚመለከቱት ነው፤ ስለሆነም በቤተሰብ ፣በመስጂድ፣ በመድረሳ፣ በትምህርት ቤት....... እና በአጠቃላይ በሙስሊሙ ማህበረሰብ ውስጥ ተግባራዊ ምሳሌ ያስፈልገናል።

ይህ ማለት ግን ተምሳሌት እስክናገኝ (እስክንሆን) ድረስ የተርቢያውን ሥራ እንተወዋለን ማለት ሳይሆን እኛ ራሳችን ወደ መልካም አርአያነት መለወጥ አለብን ለማለት ነው።

ይህ አላህ ላገራላቸው ሰዎች ቀላል ቢሆንም ነገሩ ፈታኝ ነው። ሌሎችን ከመተቸታችን በፊት ሁሌም የራሳችንን እንቅስቃሴና ባህሪ ዘወር ብለን ማስተዋል አለብን።ይህ ማለት ግን ወደ ትክክለኛው ነገር ሰዎችን አናመላክት ማለት አይደለም።

ለምሳሌ አንተ ተርቢያ ከምታደርገው ሰው (ከልጆች)አንድን ነገር ትፈልጋለህ አንተ ግን በዛ ነገር ላይ አትገኝም።ይህ ተግባርህ ልጆቹ
ላይ ጫና እንዲፈጠር ውስጣቸው የተጋጨ፣ግራ የተጋቡና የሚዋልሉ እንዲሆኑ ያደርጋቸዋል እንጂ የምትፈልገውን መስመር እንዲይዙ አያደርጋቸውም።

ወላጆች በልጆቻችሁ ላይ ልታዩት የምትፈልጉትንና የምትወዱትን ባህሪ በመላበስ ጥሩ ተምሳሌት ሁኑ።

•┈┈••••○○❁ ❁○○••••┈┈•

አላህ ትውልድን የሚያንፁ መልካም አርአያዎችን ያብዛልን ያሉትንም ይጠብቅልን።ለኛም መልካሙን ያግራልን።

#ተርቢያ #አርዐያ
@nesiha_ouserya
2.5K viewsedited  09:45
Open / Comment
2021-01-19 12:44:33
1.8K views09:44
Open / Comment
2021-01-18 09:43:29 ካልተፈቀደ እይታ አይናችሁን ስበሩ

➪«ተወርዋሪ ቀስት አካል ላይ የሚያደርሰውን አደጋ ያህል ያልተፈቀደ(ሐራም) እይታ ቀልብ ላይ አደጋ ያደርሳል። ባይገለው እንኳ ያቆስለዋል።»
ኢብኑል ቀዪም ረሂመሁሏህ
(ረውደቱል ሙሒቢን/ 97)
𝐓𝐞:http://t.me/sultan_54

#አይንን መስበር
2.0K viewsedited  06:43
Open / Comment
2021-01-17 20:27:52 በሩን በማንኳኳት ላይ ታገሱ

ፉደይል ኢብን ኢያድ አላህ ይዘንለትና እንዲህ ይላል፦

ትእግስትን ከህጻን ልጅ ተማርኩኝ

አንድ ቀን ወደ መስድጅ እየሄድኩ አንዲት እናት ቤቷ ሆና ልጇን ትገርፋለች ልጁም እየጮሀ በሩን ከፍቶ ሮጠ እናቱም በሩን ዘጋችበት ።

ከመስጅድ ስመለስ ልጁ ካለቀሰ በኋላ በሚያሳዝን ሁኔታ የቤቱ መቃን ስር ተኝቶ አገኘሁት እናቱም ልብዋ ራራና በሩን ከፈተችለት።

ፉደይልም ጺሙ በእንባ እስከሚርስ ድረስ አለቀሰ።
እንዲህም አለ

ሱብሃነላህ! ባርያው በአላህ عز وجل በር (በማንኳኳት) ቢታገስ አላህ በሩን ይከፍትለታል ።

አቡ ደርዳእ رضي الله عنه እንዲህ አለ፦
በዱአ ጠንክሩ እነሆ በሩን ማንኳኳት የሚያበዛ ሰው ሊከፈትለት ይቀርባል።
...
مصنف ابن أبـﮯ شيبة【 ٦/٢ 】

•┈┈•◈◉❒
#መልዕክት #ዱዓ
@nesiha_ouserya
2.0K viewsedited  17:27
Open / Comment
2021-01-14 09:09:08 ከሚስት ሀቆች

❹ ባሏ ከእሳት ሊጠብቃት

(يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا قُوا أَنْفُسَكُمْ وَأَهْلِيكُمْ نَارًا) [التحريم:6].
"እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ነፍሶቻችሁንና ቤተሰቦቻችሁን መቀጣጠያዋ ሰዎችና ደንጋዮች ከኾነች እሳት ጠብቁ፡፡" ተህሪም 6
 
እንደዚሁም በሰላት ሊያዛት

(وَأْمُرْ أَهْلَكَ بِالصَّلَاةِ وَاصْطَبِرْ عَلَيْهَا) [طه:132]
"ቤተሰብህንም በስግደት እዘዝ፡፡ በእርሷም ላይ ዘውትር፤(ጽና)፡፡ " ጣሃ 132

➬ይህም ማለት ዲናዊ እውቀትን ሊያስተምራት በመልካም ሊያዛት ከመጥፎ ሊከለክላት ሲሆን፤ባጭሩ በአኼራ ከጀሀነም እሳት ተጠብቃ ጀነትን የምትወርስበትን መንገድ ያመቻችላታል ።

ወንድ (ባል)የቤተሰቡ አርዓያ እንደመሆኑ በሁሉም ሁኔታው ከቤተሰቡ አባላት የተሻለ ሊሆን ይገባል።

➬ ወንዱ በተግባር ወይም በእውቀት ከዲን የራቀ ሲሆን ቤተሰብ ብሎም ትውልድ እንዲበላሽ ምክንያት ይሆናል።

ሰዎችን ከምንቀርፅበት አደገኛው መንገድ መጥፎ አርዐያነት ነው።

➬ይህን በተመለከተ ፉደይል ኢብን ዒያድ እንዲህ ይላል፦ማሊክ ኢብኑ ዲናር ሰላቱን ሳያስተካክል የሚሰግድ ሰው ይመለከትና "ለቤተሰቦቹ አዘንኩላቸው" ይላል። "እሱ ሰላቱን ያበላሻል አንተ ለቤተሰቦቹ ታዝናለህ" አሉት።
ማሊክም "እሱ ትልቃቸው ነው ከሱ ነው የሚማሩት" ብሎ መለሰላቸው።

ወንዱ የአላህን ድንበር የሚያስጠብቅ ሳይሆን እራሱ ድንበር የሚተላለፍ፣ በቤቱ አዛዥ መሆኑ ቀርቶ ታዛዥ ሲሆን፣እሱን የሚከተሉት ሳይሆን ተከታይ መሆኑ ደግሞ ሌላው ሙሲባ ነው።
•┈┈••••○○❁ ❁○○••••┈┈•

ያ አላህ! ቤተሰብ ይስተካከል ዘንድ የቤተሰብ ሀላፊዎችን አስተካክልልን።

@nesiha_ouserya
#ትዳር #የሚስት ሀቅ
2.3K viewsedited  06:09
Open / Comment